ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ የተለያዩ የስፖርት ማቴሪያሎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 002/2018 ዓ.ም
ድርጅታችን የተለያዩ የስፖርት ማቴሪያሎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም ተጫራቾች፡-
- የታደሰ ፍቃድና የዘመኑ ግብር ለመክፈላችሁ መረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
- የማይመለስ ቫትን አካቶ በብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሠነዱን መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ገንዘብ ቤት ቢሮ ቁጥር 004 በመቅረብ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
- ፋይናንሻል ሰነድ እና ቴክኒካል ሰነድ ኦሪጅናል እና ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። የሚቀርበው ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን አለመሆኑ በግልጽ መቀመጥ አለበት።
- ለጨረታ ዋስትና የሚሆን የሚያቀርቡትን አጠቃላይ ዋጋ 2% በሲፒኦ ለብቻው በኢንቨሎፕ በማሸግ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ዋጋ ላቀረቡባቸው የስፖርት ማቴሪያሎች ናሙና ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ሠነዶች ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሠዓት መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ግዥ ቢሮ ቁጥር 503 ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ጨረታው በዚያው ዕለት ከጠዋቱ 4፡15 ሠዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ፖ.ሣ.ቁ. 3516 ስልክ ቁጥር 011-369-0563 ፋክስ 011-551-3299
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
