በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በሰሜን ሸዋ ዞን የመሀል የሜዳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የG+3 ህንፃ ግንባታ የዲዛይን ሥራ አማካሪ ድርጅት አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የG+3 የህንፃ ግንባታ የዲዛይን ሥራ እና የማማከር አገልግሎት ግዥ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በሰሜን ሸዋ ዞን የመሀል የሜዳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የG+3 ህንፃ ግንባታ የዲዛይን ሥራ አማካሪ ድርጅት አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም ደረጃ 2 እና ከዚያ በላይ የሆነ የግንባታ ሥራ ዲዛይን እና የማማከር አገልግሎት ህጋዊ የሥራ ፈቃድ ወይም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው ተጫራች መጫረት/መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በሰ/ሸዋ ዞን የመሀል የሜዳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በጨረታ ለሚገዛው የግንባታ ሥራ ዲዛይን እና የማማከር አገልግሎት ተጫራቾች የ2018 ዓ.ም የታደሰ እና አግባብነት ያለው የሥራ ፍቃድ በተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበ እና በቅርብ ጊዜ የታክስ ክሊራንስ ሰርተፍኬት ያለው እና ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል እና ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በወጣበት በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በሰሜን ሸዋ ዞን መሀል የሜዳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በመሀል ሜዳ ከተማ የG-3 ቅይጥ አጠቃቀም ህንፃ ዲዛይን /G+3 mixed use Building/ ሥራ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በመ/ሜዳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገ/ድርጅት ቢሮ ቁጥር 2 የሚያገኙት ሲሆን የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አየር ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ በሥራ ሰዓት የማይመለስ 800.00 ብር በመክፈል የመጫረቻ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- የህንፃ ዲዛይን ሥራ እና የማማከር አገልግሎቱ 2ተኛ ደረጃ እና ከዚያ በላይ ያላችሁ ተጫራቾች ዋናውን እና ኮፒውን የመጫረቻ ሰነድ የታደሰ ንግድ ፈቃድ እና ለውድድር አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በሙሉ በታሸገ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ተጫራቾች በግዥ ፈፃሚ ድርጅት ስም የተዘጋጀ የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ መጫረቻ ዋጋውን 2% በCPO /ሲፒአ ወይም ቅድመ ሁኔታ በሌለው የባንክ ዋስትና ከብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ/ በማይበልጥ በዋናው የቴክኒክ ፕሮፖዛል ውስጥ በማካተት መቅረብ አለበት።
- ቴክኒካል እና ፋይናንሺያል ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ በአንድ ኮፒ እና ኦሪጅናል፣ በሁሉም ሰነዶች ፊርማ፣ የአማካሪ ድርጅት አድራሻ እና ስም፣ የባለቤቱ አድራሻ እና ስም እንዲሁም ለተጫራቾች በተሰጠው መመሪያ እና የመጫረቻ ሰነድ ላይ እንደተመለከተው መቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አየር ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት የመጫረቻ ሰነዱን በመ/ሜዳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገ/ድርጅት ቢሮ ቁጥር 2 በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው ። የጨረታ ሳጥኑ በእለቱ 5፡00 ሰዓት ታሽጎ 5፡30 ይከፈታል፡፡
- የመ/ሜዳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ጨረታውን በሚመለከት ግልፅ ያልሆነ ነገር ካለ በስልክ ቁጥር 0909322641 ወይም 0116851335 ደውለው በመጠየቅ መረጃ ማግኘት ይችላሉ።
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በሰሜን ሸዋ ዞን የመሀል ሜዳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት
