የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት አመት ለሴክተር መስሪያ ቤቶች በኤሌክትሪክ ቻርጅ የሚሰራ ሞተር ሳይክል ግዥ በዘርፉ የተሰማሩ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት አመት ለሴክተር መስሪያ ቤቶች በኤሌክትሪክ ቻርጅ የሚሰራ ሞተር ሳይክል ግዥ በዘርፉ የተሰማሩ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም፡-
- የዘመኑን የታደስ የንግድ ስራ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችል
- የአቅራቢነት ምዝገባ ሠርተፊኬት ማቅረብ የሚችል
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 70,000 (ሰባ ሺ) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንከ ጋራንቲ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ሰነዱን ከስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 3 በመቅረብ የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ) ብር ብቻ በመክፈል መግዛት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን፣ ሰነዱን በሚገባ በመሙላት ፋይናንሻል አንድ ኦርጂናል እና 2ኮፒ ለየብቻ እንዲሁም ቴክኒካል ዶክመንቱን አንድ ኦርጂናል እና ሁለት ኮፒ ለየብቻ በታሽጋ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ሳጥኑ በ15ኛው ቀን በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ 8፡30 ሰዓት መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ 15ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች ያቀረቡት የቸረታ ዋስትና ከተጠየቀው ዋጋ አንሶ ከተገኘ ከጨረታው ይሰረዛል፡፡
መምሪያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0467710586
የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
