Tender Detail

Tender Details

  • Company Ethiopian Athletics federation (የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን)
  • Address ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንጻ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0116-47-97-94
  • Websitehttps://eaf.org.et/
  • Deadline20 Nov 2025, 12:00 AM
  • magazineሪፖርተር
  • Bid Document Price
  • opening date2025-11-20 00:00:00
  • Categories Gift Items , Awards and Recognition Items

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በ2018 በጀት ዓመት በሚያካሂዳቸው የሀገር ውስጥ ውድድሮች አገልግሎት ላይ የሚውሉ የተለያየ መጠን ያላቸውን ደረጃውን የጠበቀ የሜዳሊያ፣ የዋንጫ እና ሪቫን ግዥ በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


 

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

 

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 2018 በጀት ዓመት በሚያካሂዳቸው የሀገር ውስጥ ውድድሮች አገልግሎት ላይ የሚውሉ የተለያየ መጠን ያላቸውን ደረጃውን የጠበቀ የሜዳሊያ፣ የዋንጫ እና ሪቫን ግዥ በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

በዚሁ መሠረት-

  1. በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የቲን እና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ
  2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው
  3. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውንና ኮፒውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል
  4. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስረኛው ቀን 400 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት 430 ሰዓት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 (መስብሰቢያ አዳራሽ) ይከፈታል
  5. ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዕቃዎች ለእያንዳንዱ ዕቃ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ እና ላምፕል ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል
  6. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል
  7. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
  8. ተጫራቾች የሚጫረቱት በዘርፉ የተሰማሩ መሆን አለባቸው

ድራሻ:- ጉርድ ሾላ ዴሬሽን ሕንጻ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6

ለበለጠ መረጃ:- 0116-47-97-94/0116-47-95-78 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ

                 ፋክስ  0116-45-08-79 .. 13336

 

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

 

Save Tender