የወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት በወራቤ ሆስፒታል ለባዮ ጋዝ /BIOGAS/ ስራ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት በወራቤ ሆስፒታል ለባዮ ጋዝ /BIOGAS/ ስራ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በዘርፉ ፈቃድ ያላቸው W.C-5. /G.C-6 እና ከዚያ በላይ የሆኑ ተጫራቾችን
1. የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ እና የተጨማሪ እሴት ታከስ የምዝገባ ሰርተፊኬት የሚያቀርቡ::
2. የንግድና የሥራ ፈቃድ በጀት ዓመት የታደሰ ያላቸውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
3. የኮንስትራክሽንና ከተማ ልማት ሚኒስቴር የዘመኑን ምዝገባ ሰርተፍኬት የሚያቀርቡ ::
4. የጨረታ ዋስትና 40000 (አርባ ሺህ) ማስያዝ የሚችሉ ሲሆን ለስድስት ወር የጸና መሆን አለበት:: ከዛ በታች ከሆነ ውድቅ ይደረጋል፡፡
5. የመስራት አቅም እንዳላቸው የሚገልጽ የወቅቱን የባንከ እስቴትመንት እና የስራ ልምድ ብቃት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
6. የዚህ ጨረታ ተካፋዮች በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚ/ር በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው::
7. የኦዲት ሪፖርት እና የድርጅቱ አወቃቀርንና ከዚህ በፊት የሰራቸውን ስራዎች የሚገልጽ የስራ ልምድ ማቅረብ የሚችል ተቋራጮች ሰነዱን ከወራቤ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይድ ሆስፒታል ቢሮ ቁጥር 302 በመቅረብ ለሰነድ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን የጨረታ ሰነዱን ፋይናንሺያል ዶክመንት በሚገባ በመሙላት አንድ ኦርጅናልና 2 ኮፒ ለየብቻ ቴክኒካል ዶከመንትን አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ባሉት 21 ተከታታይ ቀናት በኃላ ባለው የስራ ቀን ውስጥ ከ8፡00 ሰዓት ድረስ በግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ከፍል 302 ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ሳጥኑ በዚሁ እለት በ08:00 ታሽጎ ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ-
- የተወዳዳሪ ያቀረቡት የጨረታ ዋስትና ከተጠየቀው ዋጋ አንሶ ከተገኘ ከጨረታው ይሰረዛል፡ ፡
- የተወዳደሪ ተጫረቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው አለመገኘት የጨረታ መከፈቻ ቀን አይለውጠውም፡፡
- *ሆስፒታሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0920057024/0913213696 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
