የአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን አገልግሎት ለሚሰጣቸው ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ነገሮችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን አገልግሎት ለሚሰጣቸው ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል፡-
- ሎት 1፡- የመንገድ ጥገና ሥራ
- ሎት 2፡- ቧንቧና የቧንቧ መገጣጠሚያ እቃዎች
- ሎት 3፡- የሕንፃ መሳሪያ
- ሎት 4፡- የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ሕጋዊና በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድና ከመንግሥት የሚጠበቅባቸውን የዘመኑን ግብር የከፈሉና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ።
- በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ /100/ አንድ መቶ ብር በመክፈል 4/03/2018 ዓ.ም እስከ 19/3/2018 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 1 ድረስ በመምጣት መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነዱ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ላይ እና ዋጋው መሙያው ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፊርማ በግልጽ በማስቀመጥ ለዚህ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይቻላል።
- የጨረታ ሳጥኑ በ19/03/2018 ዓ.ም 4፡01 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸውን በተገኙበት በዚሁ ቀን 19/3/2018 ዓ.ም 4፡30 ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታው ማስከበሪያውን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው የታወቁ ባንኮች የሚሰጥ እንደ ተጫራቾቹ ምርጫ የጠቅላላ ዋጋውን 2% በጥሬ ገንዘብ /CPO/ ወይንም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል።
- የጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ገንዘብ ለተሸናፊዎች አሸናፊ ውል ከፈጸመ በኋላ የሚመለስ ሲሆን ለአሸናፊው ድርጅት ውል ፈጽሞ 10% የውል ማስከበሪያ እንዳስያዘ የጨረታ ማስከበሪያው ይመለስለታል።
- አሸናፊው ተጫራች ማሸነፋ ከተገለጸለት ከ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ውል መግባት ይጠበቅበታል፤ ያስያዘው 10% የውል ማስከበሪያ ያሸነፈበትን እቃ ሙሉ በሙሉ አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን መጋዘን ካስረከበ ከ30 ቀናት በኋላ ይመለስለታል።
- በሎት 1፣2፣3፣ 4 የምትወዳደሩ ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
- መ/ቤቱ የሚገዛውን እቃ ብዛት 20% የመጨመርና የመቀነስ መብት አለ።
- መ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብት አለው።
- ተጨማሪ መረጃዎችንና የጨረታ ሰነድ አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቁጥር 01 ማግኘት ይችላሉ።
- ውድድሩ የሚደረገው በእያንዳንዱ ሎት በጥቅል ድምር ዋጋ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 033 444 0562/ 033 444 0011 ይጠይቁ።
ማሳሰቢያ፡- የመክፈቻው ቀን በዓል ላይ ከዋለ በሚቀጠጥለው በሥራ ቀን ከላይ በተገለፀው ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
በሰሜን ሸዋ ገንዘብ መምሪያ የአንፃኪያ ገምዛ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
