Tender Detail

Tender Details


ንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የጨረታ ቁጥር 2/2018 ዓ.ም ለስልጠና እና ለገፀ ምድር ማልማትና ማስዋብ ስራ ግዥ ለመፈጸም 2ኛ ዙር የሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት እና ለማሰራት ይፈልጋል።


 

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

 

ንፋስ ስል ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የጨረታ ቁጥር 2/2018 . ለስልጠና እና ለገፀ ምድር ማልማትና ማስዋብ ስራ ግዥ ለመፈጸም 2 ዙር የሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት እና ለማሰራት ስለሚፈልግ፦

  1. የገፀ ምድር ማልማትና ማስዋብ ስራዎች
  2. የስልጠና ማሽነሪ ጥገና ስራዎች
  3. የኮንስትራክሽን ስልጠና እቃዎች
  4. የከተማ ግብርና እቃዎች እና የእንስሳት መኖዎች

ከላይ የተዘረዘሩትን ዕቃዎች አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ የጨረታው መስፈርቶች፡-

  1. ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
  2. ተጫራቾች በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መኖራቸውን የሚያረጋግጥ የምስ ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
  3. ተጫራቾች የግብር ከፋይ ቁጥር (Vat) ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
  4. Tin No ሰርተፍኬት እና የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል
  5. ለጨረታ የሚሆን ሊራንስ ያለው
  6. የተሰማራበት ስራ ኢንተርፕራይዝ ከሆነ 2018 . የታደሰ የደረጃ እድገት ያላቸው
  7. ደረጃ ሰባት ሆኖ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ስራ ዘርፍ የሆነና የገፀ ምድር ማስዋብ ስራ ላይ የተሰማራ
  8. ኢንተርፕራይዝ ከሆነ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት LMIS ሙሉ መረጃቸው የተመዘገበ መሆን አለባቸው
  9. ስድስት ወር ያልሞላው ከስራው ጋር ተዛማጅነት የሆነ መልካም የስራ አፈፃፀም ደብዳቤ ከመንግስት ተቋም ማቅረብ የሚችል
  10. ተጫራቾች ወቅታዊ የገበያ ዋጋን ያገናዘበ ስራ ዝርዝር ማለትም ከገበያ ዋጋ የተጋነነ ነጠላ ዋጋ (unit rate) በከፍታ ወይም በዝቅታ ተሞልቶ ካገኘ የስራው ተቋራጮች (cost break down) ሰርተው እንዲያቀርቡ ያስገድዳል።
  11. ተጫራቾች በስራው ዝርዝር በሙሉ ሆነ በአንዳንድ ተራ ቁጥር ላይ ዋጋ አለመሙላቱ (unfilled rate) ከተገኘ ስራውን በራሱ ወጪ እንደሚሰራ ይወሰዳል።
  12. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከማስገባታቸው በፊት የገፀምድሩን ሳይት ማየት አለባቸው።
  13. ተጫራቾች ከላይ የተዘረዘሩትን የግዥ ዓይነት (ሎቶች) ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን በባንክ የተመሰከረለት ፍያ ትዕዛዝ (CPO) ወይም የፕሮጀክት ዋጋ 2% ማቅረብ የሚችሉና የዋስትና ደብዳቤ ከተደራጀበት ወረዳ ማቅረብ የሚችል። በባንክ ጋራንቲ እና የዋስትና ደብደቤ Nifas Silk poly Technic Collage (ንፋስ ስልክ ፖሊ ኒክ ኮሌጅ) በሚል በማሰራት ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  14. የበጎ አድራጎት ስራ ላይ የተሳተፉ
  15. ማሽነሪ ማቴሪያል እስኬጁል ማቅረብ የሚችል
  16. ስራውን ለመስራትና በተሰጠው ጊዜው ለማጠናቀቅ ቃለ ማቅረብ ይኖርበታል።
  17. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ለእያንዳንዱ ሎት በመፈል የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ንፋስ ስልክ ፖሊ ኮሌጅ መውሰድ ይችላል።
  18. ጨረታው 11ኛው የሥራ ቀን ጠዋት 400 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ቀን 430 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ ይከፈታል። የመፈቻው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል።
  19. ተጫራቾች በገዙት ጨረታ ሰነድ ላይ ዋጋ ሞልተው በታሸገ ኤንቨሎፕ ፋይናንሻል ኦርጅናልና ኒካል ኦርጅናል በአንድ ፖስታ፣ ኮፒውን ፋይናንሺያል እና ቴክኒካል በአንድ ፖስታ በማድረግ በጠቅላላ 2 በታሽገ ፖስታ በማድረግ ለመንግስት ግዥ ዳይሬቶሬት ቢሮ ቁጥር 101 ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  20. ጨረታ ሰነድ ላይ የድርጅቱን ሕጋዊ ማህተም እና ፊርማ አድርጎ የማያቀርብ ማንኛውም ተጫራች ከጨረታው ውጪ ይሆናል።
  21. ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ናሙና ለተጠየቀባቸው ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ አለባቸው። ጨረታ ከተከፈተ በኋላ ናሙና ማቅረብ አይቻልም። ናሙና ለተጠየቀባቸው ዕቃዎች ናሙና ያላቀረበ ተወዳዳሪ ተጫራች ከውድድር ወጪ ይሆናል።
  22. ተጫራቾች ለጨረታ በሚመጡበት ጊዜ ህጋዊ ሰነድ ይዞ ማቅረብ ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያና ህጋዊ ውክልና ያላቸው መሆን አለባቸው።
  23. ተራ ቁጥር 67910111213141516 ላይ የተጠቀሰው መስፈርት ለገፀ ምድር ማልማት እና ማስዋብ ስራ ተጫራቾች ሲሆን ከተጠቀሱት ተራ ቁጥር ውጪ ያሉት ለሁሉም ሎቶች ግዴታ ሆኖ ያገለግላል።
  24. ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

 

አድራሻ፡- አዲስ አበባ ጎተራ ኦይል ሊቢያ ዴፖ አጠገብ

ስልክ ቁጥር፡- 0114-70-70-78

 

የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

 

Save Tender