በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የመርሐቤቴ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የመንገድ ስራ የማሽን ኪራይ በግልፅ ጨረታ አጫርቶ መከራየት እና ከዚህ በፊት የመ/ወ/አስ/ፅ/ቤት G+5 ህንፃ ግንባታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በ27/02/2018 ዓ/ም በደረጃ 4Gc/Bc እና በላይ ባሉ ኮንትራክተሮች ለማስገንባት ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወቃል::
የጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የመርሐቤቴ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የመንገድ ስራ የማሽን ኪራይ በግልፅ ጨረታ አጫርቶ መከራየት እና ከዚህ በፊት የመ/ወ/አስ/ፅ/ቤት G+5 ህንፃ ግንባታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በ27/02/2018 ዓ/ም በደረጃ 4Gc/Bc እና በላይ ባሉ ኮንትራክተሮች ለማስገንባት ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወቃል:: ስለሆነም የደረጃ ማስተካከያ ማድረግ ስለተፈለገ በደረጃ 3Gc/2Bc እና ከዚያ በላይ ያሉ ኮንትራክተሮች በሚል የተስተካከለ መሆኑንና የጨረታ ፖስታ አስተሻሸጉን በተመለከተም ቴከኒካል ፖስታ ኦርጂናልና ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሺያል ፖስታ ኦርጂናልና ኮፒ ለየብቻው መታሸግ ያለበት ሲሆን ሌሎች ማስታወቂያው ላይ የተጠቀሱት ግን ያልተቀየሩ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የመንገድ ስራ ማሽን ኪራዩን በተመለከተ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደርየሚችሉ መሆኑን እየገለፃን ፡፡
1. በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ፣ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና ቲን ነምበር ኮፒውን በፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. የሞሉት ዋጋ ከ200,000 ሺህ ብር በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታከስ (VAT) ከፋይ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
3. እያንዳንዱን የጨረታ ሰነድ የመንገድ ስራ ማሽን ኪራይ በብር 300 (ሶስት መቶ ብር ብቻ) ጨረታው ከወጣበት ቀን እስከ 15ኛው ቀን 11፡30 ሰዓት ድረስ ባሉት የካላንደር ቀናት ውስጥ ከቢሮ ቁጥር 05 መግዛት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በቁርጥ 50,000 ብር /ሃምሳ ሺህ ብር ብቻ/ በባንክየተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ወይም በመ/ቤታችን የውስጥ ገቢ ደረሰኝ ማስያዝ አለባቸው፡፡
5. የጨረታ ውድድሩ የሚካሔደው በግዥ መመሪያው መሰረት ይሆናል፡፡
6. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን ዋናውን በአንድ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማድረግ በመ/ወ/ገንዘብ/ጽ/ቤት በግዥና ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 08 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን እስከ ጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ጨረታው የሚከፈተው በ16ኛው ቀን በ3፡01 ሰአት ታሽጐ በ3፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
8. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
9. በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 08 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 011-13-20-136/005 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ፡- የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀን እሁድና ቅዳሜ ወይም ህዝባዊ በዓል ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
በሰሜን ሸዋ ዞን የመርሐቤቴ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
