በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በመደበኛ በጀት ለገ/ጉ/ወ/ወረዳ የኮንበል ማዘጋጃ ቤት የደረቅ ቆሻሻ ጉድጓድ ግንባታ እና ለገ/ጉ/ወ/ወረዳ ለፖሊስ ጽ/ቤት የቢሮ ጥገና ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ሀገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ መለያ ቁጥር GGWW/07/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በመደበኛ በጀት ለገ/ጉ/ወ/ወረዳ የኮንበል ማዘጋጃ ቤት የደረቅ ቆሻሻ ጉድጓድ ግንባታ እና ለገ/ጉ/ወ/ወረዳ ለፖሊስ ጽ/ቤት የቢሮ ጥገና ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ስለሆነም ተጫራቾች
- CPO ለደረቅ ቆሻሻ ጉድጓድ 25,000 (ሀያ አምስት ሺ ብር)
- CPO ለቢሮ ጥገና 25,000 (ሃያ አምስት ሺ ብር)
1. የዘመኑን ንግድ ፍቃድ ያሳደሱ የቫት እና ቲን ነምበር ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ የመወዳደሪያ ደረጃቸውም GC/Bር ደረጃ 8 እና ከዛ በላይ የሆኑ ተቋራጮች
2. ከገቢዎች መስሪያ ቤት የኦዲት ክሊራንስ ማምጣት የሚችሉ
3. ተወዳዳሪዎች የቫት 7.5% ተቀናሽ ለማድረግ ፍቃደኛ መሆን አለባቸው
4. በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሚዝዙት ጨረታ ሰነዱን ጠቅሰው በማመልከቻ ሲጠይቁ የድርጀቱ ባለቤት መሆን አለባቸው። እንዲሁም በውክልና ሰነዱን መውሰድና መወዳደር አይቻልም።
5. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 1ኛው ተከታታይ ቀናት እስከ 8፡00 ሰአት ድረስ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል የጨረታውን ሰነድ መሀል አምባ ገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ድረስ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ።
6. የጨረታ ማስከበሪያ በባንከ የተረጋገጠ ሲፒኦ በገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ስም ማሰራት አለባቸው። ውል የሚጸናው ለ90 ቀናት መሆኑን እገልጻለን።
7. ተጫራቾች የጨረታውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ዶክመንት ሀ/ ለቴክኒካል ዶክመንት አንድ አርጅናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒ በማድረግ ቴክኒካል በሚል በመለየት ለ/ ለፋይናንሻል ዶክመንት አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒ በማድረግ ፋይናንሻል በሚል በመለየት በሰም በማሸግ ከላይ በተጠቀሰው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ/ ከባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከቴክኒካል ኦርጅናል ዶከመንቱ ጋር በማድረግ በሰም በማሸግ ቴክኒካል ዶክመንት በሚል በመለየት ይህ ማስታወቂያ እየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 (አስራ አምስት) ተከታታይ ቀናት መሀል አምባ የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ድረስ በመምጣት ለጨረታ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
8. የጨረታው ሰነድ በ15ኛው ተከታታይ ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይታሸጋል። ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
9. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ፡- 1. በአፈፃፀም ምክንያት ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ድርጅቶች መወዳደር አይችሉም።
2. ተጫራቾች ተጫርተው ከአሸነፉ በኋላ አገልግሎታቸው ጥራት ያለውና ቀልጣፋ ካልሆነ የውል ጊዜ የምናቋርጥ መሆኑን እንገልፃለን።
3. ጨረታ የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘዋወራል።
4. በወረዳሁ ውስጥ አንድ እና ከዛ በላይ ፕሮጀክት የያዘ አካል መወዳደር አይችልም።
5. ተወዳዳሪዎች ከአሸነፉ በኋላ ቅደመ ክፍያ ሳይጠይቁ ስራውን መስራት የሚችሉ መሆን ፣
ለበለጠ መረጃ፡- የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት የቢሮ ስልክ ቁጥር 0113360631/446 ይደውሉ።
ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
መሀል አምባ
