Tender Detail

Tender Details


አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ በግዥ መለያ ቁጥር, አአከአአድ/ብግጨቁ/021/2018 የሴኪሪቲ ካሜራዎች (ሎት 1) ፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች (ሎት 2)፣ የቢሮ ፈርኒቸር (ሎት 3) እና የኮንስትራክሽን ዕቃዎች (ለህንጻ ጥገና) (ሎት 4) አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


 

የብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

 

አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ በግዥ መለያ ቁጥር, አአከአአድ/ብግጨቁ/021/2018 የሴኪሪቲ ካሜራዎች (ሎት 1) የኤሌትሮኒክስ ዕቃዎች (ሎት 2) የቢሮ ፈርኒቸር (ሎት 3) እና የኮንስትራክሽን ዕቃዎች (ለህንጻ ጥገና) (ሎት 4) አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም በመስኩ የተሰማሩና ጋዊ ፈቃድ ያላቸው አቅራቢዎች (ድርጅቶች) ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን፡-

  1. በዘርፉ የተሰማራ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ኮፒ (Valid Trade Licensee)
  2. በመንግስት ግዥ ላይ ለመሳተፍ የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ስለመግባቱ በድረ-ገፅ የተመዘገበበት ኮፒ፣
  3. የታከስ ከፋይ የምዝገባ ሰርተፍኬት፣
  4. የተጨማሪ እሴት የምዝገባ ሰርተፊኬት ኮፒ (VAT Certificate)
  5. በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የታደሰ ፈቃድ (Valid Tax Clearance Certificate)
  6. የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ወይም የባንክ ጋራንቲ ለሎት 1 (የሴኪሪቲ ካሜራዎች) ብር 300,000.00 (ሶስት መቶ ሺህ) ለሎት 2 (የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች) 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ) ለሎት 3 (የቢሮ ፈርኒቸር) ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ) እና ለሎት 4 (የኮንስትራክሽን ዕቃዎች - ለህንጻ ጥገና) ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ) በማቅረብ በግልፅ ጨረታው ላይ መወዳደር ይችላሉ።

በጨረታው መወዳደር የሚፈልጉ አቅራቢዎች (ድርጅቶች) ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ እና ቅዳሜ እስከ ምሳ ሰዓት (600 ሰዓት) የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በጥሬ ገንዘብ በመፈል በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ 22 እየሩስ ህንጻ ከሚገኘው የድርጅቱ ዋናው /ቤት (ማዕከል) የግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 7-02 ወይም 7-01 መውሰድ ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን ኒካል እና ፋይናንሻል ዶክመንት በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦሪጅናል እና ኮፒ በመለየት እስከ ህዳር 30 ቀን 2018 . ጠዋት 400 ሰዓት ድረስ በግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 7-02 ለጨረታው በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

ጨረታው ህዳር 30 ቀን 2018 . ጠዋት 400 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ጠዋት 430 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት በግዥ ዳይሬከቶሬት ቢሮ ቁጥር 7-02 ይከፈታል።

ማሳሰቢያ፤

ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ስልክ ቁጥር፡ 0118 21 22 14

 

የአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት

 

Save Tender