አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ በግዥ መለያ ቁጥር አአከአአድ/ብግጨቁ/018/2018 የጽህፈት መሳሪያዎች (ሎት 1)፣ የጽዳት ዕቃዎች (ሎት 2)፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎች እና ግብዓቶች (ሎት 3)፣ የመስተንግዶ ዕቃዎች (ሎት 4) እና የተሽከርካሪ ንፅህና መጠበቂያ ግብዓቶች (ሎት 5) አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ በግዥ መለያ ቁጥር አአከአአድ/ብግጨቁ/018/2018 የጽህፈት መሳሪያዎች (ሎት 1)፣ የጽዳት ዕቃዎች (ሎት 2)፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎች እና ግብዓቶች (ሎት 3)፣ የመስተንግዶ ዕቃዎች (ሎት 4) እና የተሽከርካሪ ንፅህና መጠበቂያ ግብዓቶች (ሎት 5) አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በመስኩ የተሰማሩና ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸው አቅራቢዎች (ድርጅቶች) ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን፡-
- በዘርፉ የተሰማራ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ኮፒ (Valid Trade Licensee)!
- በመንግስት ግዥ ላይ ለመሳተፍ የአቅራቢዎች ዝርዘር ውስጥ ስለመግባቱ በድረ-ገፅ የተመዘገበበት ኮፒ፣
- የታክስ ከፋይ የምዝገባ ሰርተፍኬት፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፊኬት ኮፒ (VAI Certificate)፣
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የታደሰ ፈቃድ (Valid Tax Clearance Certificate)፣
- የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ወይም የባንክ ጋራንቲ ለሎት 1 (የጽህፈት መሳሪያዎች) ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ)፣ ለሎት 2 (የጽዳት ዕቃዎች) ብር 400,000.00 (አራት መቶ ሺህ)፣ ለሎት 3 (የኢንፎርሜሽን ቴከኖሎጂ መሳሪያዎች እና ግብዓቶች ብር 300,000.00 (ሶስት መቶ ሺህ)፣ ለሎት 4 (የመስተንግዶ ዕቃዎች) ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) እና ለሎት 5 (የተሽከርካሪ ንፅህና መጠበቂያ ግብዓቶች) ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) በማቅረብ በግልፅ ጨረታው ላይ መወዳደር ይችላሉ፡፡
በጨረታው መወዳደር የሚፈልጉ አቅራቢዎች (ድርጅቶች) ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ እና ቅዳሜ እስከ ምሳ ሰዓት (6፡00 ሰዓት) የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በጥሬ ገንዘብ በመከፈል በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ 22 እየሩስ ህንጻ ከሚገኘው የድርጅቱ ዋናው መ/ቤት (ማዕከል) የግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 7-02 ወይም 7-01 መውሰድ ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ዶከመንት በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦሪጅናል እና ኮፒ በመለየት እስከ ህዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ሰዓት ድረስ በግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 7-02 ለጨረታው በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡
ጨረታው ህዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ጠዋት 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት በግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 7-02 ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር፡ 0118 21 22 14
የአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት
