የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነገሮች በጨረታ ቁጥር አ.ሚ.ኔ.በ.ግ.ጨ. 007/2018 ዓ.ም በግልፅ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በጨረታ ቁጥር አ.ሚ.ኔ.በ.ግ.ጨ 007/2018 ዓ.ም በግልፅ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ በመሆኑ በጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ፡-
- ሎት 1. የጋራዥ አገልግሎት ግዥ ሎት (በድጋሚ የወጣ)
- ሎት 2. ሞባይል እቃ ግዥ (በድጋሚ የወጣ) ሎት 7 ላፕቶፕ ግዥ (በድጋሚ የወጣ)
- ሎት 3. ሳወንድ ሲስተም ግዥ (በድጋሚ የወጣ) ሎት 8 የሙዚቃ መሳሪያዎች እቃ ግዥ
- ሎት 4. የፅዳት እቃዎች ግዥ (በድጋሚ የወጣ)
- ሎት 5. የብራንድግ የስጦታ እቃዎች ግዥ (በድጋሚ የወጣ)
- ሎት 6. የካሜራ መብራት እና ተዛማጅ አክሰሰሪዎች እቃ ግዥ
በጨረታ ቁጥር አ.ሚ.ኔ.በ.ግ.ጨ. 007/2018 ዓ.ም በግልፅ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ በመሆኑ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ፡-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉና በግዥ አቅራቢነት የተመዘገቡ፣
- ተጫራቾች በሚያቀርቡት እያንዳንዱ ሰነድ እና በፓስታ ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፊርማቸውን ማኖር ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ ሎት1 = 400.000 ብር፤ ለሎት2 -50,000 ብር፤ ለሎት3 50.000 ብር፤ ለሎት4 50,000 ብር ለሎት5-50,000 ብር ለሎት6-200,000 ብር ፤ ለሎት7= 100,000 ብር እና ሎት8 - 50,000 ብር በባንክ በተረጋገጠ ሲፒአ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸውል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 የስራ ቀናት ውስጥ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ቢሮ ቁጥር 6 ለሰነዱ 300 (ሶስት መቶ ብር) ክፍያ በመክፍል ዘወትር በሥራ ሰዓት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 28 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ጨረታው በ11ኛው ቀን በቀኑ 4፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን በቀኑ 4፡30 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 ይከፈታል። ሆኖም ግን የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ለመክፈት አያግደውም። የመክፈቻው ዕለት በዓል/ዕረፍት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ዋናውንና ኮፒውን /ቴክኒካል ኦሪጅናልና ኮፒ፣ ፋይናንሻል ኦሪጂናልና ኮፒ / በተለያየ ፖስታ በማሸግ በዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
- በአንዱ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው።
- በጨረታ ያሸነፈ ተጫራች ከመ/ቤታችን ጋር ጨረታውን እንዳሸነፈ ካወቀበት ጊዜ አንስቶ በ15 ቀናት ውስጥ በሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን 10 በማስያዝ ውል መዋዋል ይኖርበታል።
- ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ 5 ኪሎ ቅድስት ማሪያም ቤ/ክርስቲያን ከማህበረ ቅዱሳን ጀርባ ያለው ህንፃ።
ለበለጠ መረጃ ስልክ 011 1116382 መደወል ይችላሉ።
የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ
