በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር የመ/ል/ድ/አስ/ባለ/ግልጽ ጨረታ 002/2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ስለሆነም፡-
ሎት ሎት 1……. ህትመት
ሎት2…………... ፈርኒቸር፣
ሎት 3 ………. ቋሚ የቢሮ እቃዎች ኤሌከትሮኒከስ ለካሜራ የሚያስፈልጉ እና ሌሎችም
ሎት4…………. አላቂ የቢሮ እቃዎች
ሎት5…………. የፕሪንተር ቀለም
ሎት6…………. የተሽከርካሪ ቴፕ የዳሽ ቦርድ ቅባት እና ሌሎችም
ሎት 7……….የተፈጥሮ አበባ ከነማስቀመጫው
- ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በፋይናንስ ቢሮ ዌብሳይት ላይ በአቅራቢዎች ሊስት ላይ የተመዘገቡ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በ CPO ማስያዝ አለባቸው፡፡
ሎት 1....................ብር 1,000.00 / አንድ ሺህ ብር/
ሎት 2……………ብር 3,000.00 / ሶስት ሺህ ብር/
ሎት 3……………ብር 10,000.00 / አስር ሺህ ብር/
ሎት 4……………ብር 3.000.00 / ሶስት ሺህ ብር/
ሎት 5……………ብር 3,000.00 / ሶስት ሺህ ብር/
ሎት 6……………ብር 3.000.00 / ሶስት ሺህ ብር/
ሎት 7……………ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር /
- ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ ሆነው ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉና መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡
- የጨረታ አሸናፊ አሸናፊነቱን ሲገለፅለት ያሸነፈበትን ከጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በCPO ማስያዝ አለባቸው::
- ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመከፈል ፒያሳ ከሚገኘው ዋስትና የንግድ ማእከል ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 4/06 ፋይናስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ድረስ የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ዋናውን እና ኮፒ በታሸገ ኢንቨሎኘ በማደረግ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ከኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰአት ድረስ ስምንተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 03/8 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው የሚዘጋበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያ በወጣ በዘኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጐ በዚሁ ቀን ጠዋት 4፡30 ሰአት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም በሌሉበት በመ/ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ 4ኛ ፎቅ ይከፈታል፡፡
- መስሪያ ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ይሁን ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- ፒያሳ ከሚገኘው ዋስትና የንግድ ማዕከል ህንፃ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለሥልጣን
ለበለጠ መረጃ፦ በስልክ ቁጥር 01124485 መደወል ይችላሉ::
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን
