በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ለሴክተር መ/ቤቶች ሞተር ሳይክሎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ለሴክተር መ/ቤቶች ሞተር ሳይክሎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
- የታደሰ የዘርፉ ንግድ ሥራ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ እና የአቅራቢነት ምዝገባ ምስከር ወረቀት ያላችሁ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ በባንክ የተረጋገጠ 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ ለብቻ ከግዴታ ሰነዶች ጋር አሽገው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን በተጫራቾች መመሪያ መሰረት ተሞልቶ የእቃዎቹን ዋጋ መሙያ ሰነድ ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ ለብቻው በማሸግና እንዲሁም የግዴታ ሰነዶችን ከጨረታ ማስከበሪያ ጋር ለብቻው በአንድ ፖስታ ውስጥ በማድረግ በሁሉም ዶክመንት ላይ ህጋዊ የሆነ የድርጅቱ ማህተም በማሳረፍ እና አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በመሙላት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በወንዶ ገነት ከተማ ገቢዎች ቅ/ጽ/ቤት ከፍለው የከፈሉበትን ደረሰኝ በማሳየት የጨረታ ዶክመንቱን ከወንዶ ገነት ከተማ ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት መውለድ ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሳጥኑ ጋዜጣው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለ15 አስራ አምስት ተከታታይ የስራ ቀናት እስከ መጨረሻው ቀን 11፡30 ድረስ ሲሸጥ ይቆይና በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ላይ ታሽጎ በ4፡30 ሰዓት ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- በጨረታ ሰነዱ ላይ ስርዝ ድልዝ ወይም ለመለየት አሻሚ ነገር መኖር የለበትም ካለም ተጫራቹ ፓራፍ ማድረግ አለበት፡፡
- የወቅቱን ዋጋ ያላገናዘበ የጨረታ ዋጋ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ የወቅቱን ዋጋ ትንታኔ ካላቀረቡም እንዲያቀርቡ ይደረጋል፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ዕቃዎች እስከ ወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደር ፋ/ኢ/ል ጽ/ቤት ድረስ በራሳቸው ወጪ አጓጉዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡
ማሳሰቢያ፡- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
ለበለጠ መረጃ:- ስልክ ቁጥር 09 16 13 44 01/09 16 04 60 74 / ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደር ፋ/ኢ/ል ጽ/ቤት
