በጉምሩክ ኮሚሽን የአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የጉምሩክ ሕግን ተላልፈው የተያዙ የተለያዩ የኮንትሮባንድ እቃዎችን በ02/04/2018 ዓ/ም በግልጽና በሐራጅ ጨረታ በአክሽን ኢትዮጵያ (auction ethiopia) መተግበሪያ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በጉምሩክ ኮሚሽን የአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የጉምሩክ ሕግን ተላልፈው የተያዙ የተለያዩ የኮንትሮባንድ እቃዎችን በ02/04/2018 ዓ/ም በግልጽና በሐራጅ ጨረታ በአክሽን ኢትዮጵያ (auction ethiopia) መተግበሪያ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች መተግበሪያውን ከአፕ ስቶር ወይም ፕሌይ ስቶር auction Ethiopia ብለው በማውረድ www.auction.et ላይ በመመዝገብና የጨረታ ሰነዱን በማየት የሚከተሉትን ዝርዝር መስፈርቶች በማሟላት በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን፤ የእቃዎችን ሳምፕልም ከኦክሽን ኢትዮጵያ ድረ-ገጽ (auction ethiopia page) ወይም አዋሽ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በአካል በመሃኘት ወይም በቴሌግራም እንዲላክሎት በማድረግ ማየት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የጨረታ መስፈርቶች:
- ለጨረታ በቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመሳተፍ የሚያስፈልጉ ተጫራች በጨረታ በሚሸጡ ዕቃዎች ጋር በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክሰ ምዝገባ ሰርተፍኬት፤ የዘመኑን ግብር የከፈለ ስለመሆኑ ክሊራንሰ (Clearance) እና የተጨማሪ እሴት ታክሰ እንቅሰቃሴያቸውን ለታክስ ማዕከሉ ያሳወቁበት በቅርብ ጊዜ የተሰጣቸው የምሰክር ወረቀት እና የመለያ ቁጥሩን ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር አያይዞ በሲስተም አታች ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ ቀን በ02/04/2018 ዓ/ም ከኦክሽን ኢትዮጵያ ድረ- ገጽ (auction ethiopia page) ማየት ይችላሉ፡፡
- ለግልጽ ጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋሰትና (CPO) የሚወዳደሩበት እቃ ኮድ 5 በመቶ እንዲሁም ለሐራጅ ጨረታ ለሚወዳደሩበት እቃ ኮድ ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በባንክ አሰርተው በአዋሸ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ስም በማስያዝ በሲስተም አታች ማድረግ ይኖርባቸዋል።
|
ተ.ቁ |
የአጫራች ቅ/ጽ/ቤት |
የጨረታው ዓይነት |
ለጨረታ የቀረቡ እቃዎች |
የዕቃዎች መመልከቻ ቀን በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ |
የጨረታው የመዝጊያ እና የመክፈቻ ቀንና ሰዓት |
|
1 |
አዋሽ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት |
ግልፅ ጨረታ እና በሐራጅ |
ጫማዎች፣ አልባሳት፣ የመኪና መለዋወጫ ፣ የሞባይል ቀፎና አክሰሰሪ፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ምግብ ነክ ፣ የስፖርት እቃዎች፣ የእጅ ሰዓት፣ ኮስሞቲክስ፣ የስፌት ክር፣ መነፅር እና ሌሎች ልዩ ልዩ እቃዎች ፣ ኮር መሳይ ብረት፣ ሴራሚክ፣ የወዳደቀ ጎማ፣ ድንጋይና ቁራሌ፣ |
በግልፅና ለሐራጅ ጨረታ በ02/04/2018 እስከ ጠዋቱ 3:45 |
በግልፅ ጨረታ በ02/04/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሲሆን የሐራጅ ጨረታ የመጀመሪያ ጊዜ በ02/04/2018 ዓ.ም 5፡00 ሰዓት ይሆናል፡፡ |
- የጨረታው መክፈቻ ሰዓት እና ቀንን ከአክሽን ኢትዮጵያ ድረ-ገጽ (auctiction ethiopia page) በማየት የጨረታው ሂደት ተጀምሮ ከማለቁ በፊት ዋጋ መስጠት ይችላሉ፡፡
- ለጨረታው አሸናፊ ተጫሪቾች ለጨረታው ዋሰትና ያስያዙት (CPO) ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፈ ተጫራቾች ደግሞ የጨረታ ውጤት ከተለጠፈበት ቀን ጀምሮ በ3 የሥራ ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
- አሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸው በደብዳቤ ከተገለጸላቸው ቀን ጀምሮ በ3 ቀናት ውሰጥ ያሸነፈበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ዕቃውን በመረከብ ከመጋዘን ማውጣት ይኖርበታል።
- ከላይ በተ.ቁ.7 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱ ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታው ማስከበሪያ ያስያዙት ገንዘብ የከፈሉት ዋጋ ለኮሚሽኑ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለሽያጭ ይቀርባል።
- ቅ/ጽ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- የአክሽን ኢትዮጵያ (auction ethiopia) መተግበሪያ በተመለከተ የጥሪ ማእከሉን ሠራተኛ ለማግኘት ስልክ ቁጥር 09-05-11-55-11/011-66-68-828 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 09-13-97-49-27 ይደውሉ።
በጉምሩክ ኮሚሽን የአዋሽ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
