ኩባንያችን ትራኮን ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግል ማህበር ለሽያጭ አገልግሎት የሚጠቀምባቸው ኤሌክትሪካል ሚኒ ቫን መኪኖች /Electrical Mini Van/ በዘርፍ ወይም በተመሳሳይ ስራ ከተሰማሩ ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር ት/ት/ግዥ073/2018
ኩባንያችን ትራኮን ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግል ማህበር ለሽያጭ አገልግሎት የሚጠቀምባቸው ኤሌክትሪካል ሚኒ ቫን መኪኖች /Electrical Mini Van/ በዘርፍ ወይም በተመሳሳይ ስራ ከተሰማሩ ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መስፈርቶች በማሟላት እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።
- ተጫራቾች በዘርፉ ወይም በተመሳሳይ ዘርፍ የተሰማሩ 2018 ዓ.ም ህጋዊና የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያለው፣ የተ.እ.ታ ተመዝጋቢ የሆነ እና የቲን ሰርተፍኬት ያለው ማንኛዉም አገልግሎት አቅራቢ የዋጋ ማቅረቢያ ማቅረብ ይችላል ::
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ /ቢድ ቦንድ/ የጠቅላላዉን 2% ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታዉን ሰነድ ጅሞ 3 አጫሉ መንገድ አካባቢ በሚገኘዉ ትራኮን ዋና መ/ቤት ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ታህሳስ 11, 2018 ዓ.ም ድረስ የማይመለስ ብር 300 በመክፈል ሰነድ መግዛት ይቻላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ቴክኔካል እና ፋይናሻል ሰነዶቻቸዉን ለየብቻ በታሸገ ፖስታ እስከ ታህሳስ 11, 2018 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ሰአት ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታዉ ታህሳስ 11, 2018 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ሰአት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ጅሞ 3 አጫሉ መንገድ አካባቢ በሚገኘዉ ትራኮን ዋና መ/ቤት 4፡30 ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች ህንፃዎቹ በሚገኙበት ለቡ በአካል ልኪት በመዉሰድ ዋጋ መስጠት ይኖርባቸዋል።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0118722174/0911455448/
0929918416/0929040439 ግዥ ክፍል መጠየቅ ይቻላል።
ትራኮን ትሬዲንግ ኃ.የተ የግል ማህበር
