የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ ለማስፈፀም የመራጮች ምዝገባ እና ስልጠና የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት ለማከናወን የሚንቀሳቀሱ የጭነት ተሽከርካሪዎችን ለማጀብ አገልግሎት የሚውሉ ፒክ አፕ ተሽከርካሪዎች የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የእጀባ ፒክ አፕ ተሽከርካሪ ኪራይ አገልገሎት ገዥ
የጨረታ ቁጥር NEBE/NCB/08/2018
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ ለማስፈፀም የመራጮች ምዝገባ እና ስልጠና የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት ለማከናወን የሚንቀሳቀሱ የጭነት ተሽከርካሪዎችን ለማጀብ አገልግሎት የሚውሉ ፒክ አፕ ተሽከርካሪዎች የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ምድብ አንድ፡- ለመራጮች ምዝገባ የስልጠና ቁሳቁስ ስርጭት የእጀባ ፒክ አፕ ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ግዥ
ምድብ ሁለት፡- ለመራጮች ምዝገባ ቁሳቁስ ስርጭት የእጀባ ፒክ አፕ ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም
- በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ጨረታው እስከሚዘጋበት ቀን ድረስ ባሉት የሥራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 /ሦስት መቶ ብር/ በመክፈል ከቦርዱ ግዥ ሥራ ክፍል ቢሮ ቁጥር 107 ማግኘት ይችላሉ።
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ ተጨማሪ እሴት ታክስና የግብር ከፋይ ምዝገባ ሠርተፍኬት፣የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ሠርተፍኬት እና በመንግስት ኤሌክትሮኒክስ ግዥ በአቅራቢነት የተመዘገቡ ስለመሆኑ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
- የጨረታ ሰነዱን ከቦርዱ የግዥ አስተዳደር የሥራ ክፍል በመውሰድ ሞልተው አግባብ ባለው አካል በመፈረም ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ፡- ለምድብ አንድ ብር 50,000.00 (ብር ሃምሳ ሺህ ከ00/100) ለምድብ ሁለት ብር 100,000.00 (ብር አንድ መቶ ሺህ ከ00/100) በባንክ የተረጋገጠ ዋስትና ወይም ሲፒኦ ማቅረብ ይኖርበታል።
- ተወዳዳሪዎች ቴክኒካል ፕሮፖዛል እና ፋይናንሻል ፕሮፖዛል በተለያየ ፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
- ጨረታው ታህሳስ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፤
- ቦርዱ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣
አድራሻችን፡- ቦሌ ፍላሚንጎ ሬስቶራንት ገባ ብሎ
ስልክ ቁጥር፡- +251 11 515 3468
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
