በማዕከላዊ አ.ትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ ሎቶችን በመደበኛ በጀት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በማዕከላዊ አ.ትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ ሎቶችን በመደበኛ በጀት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም፡-
ሎት1 የቢሮ አላቂ እቃዎች የጨረታ መለያ ቁጥር C/E/R/S/W/l/M/D/B/Rec/Budjet/001/18/NCB፣ ሎት2 የኤሌክትሮኒክስ የጨ/መ/ቁ C/E/R/S/W/I/M/D/B/Rec/Budet/002/18/NCB፣
ሎት3 የፅዳት እቃዎች የጨ/መ/ቁ C/E/R/S/W/I/M/D/B/Rec/Budet/003/18/NCB እና ሎት4 የስጦታ እቃዎች የጨ/መ/ቁ C/E/R/S/W/I/M/D/B/Rec/Budet /004/18/NCB
ሲሆኑ፡- በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዘርፉ ላይ፣
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣
- በመስኩ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፣
- የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት የሚያቀርብ፣
- የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት የሚያቀርብ፣
- የአቅራቢዎች የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፣
የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለተራ ለሎት 1/አንድ/ 10,000/አስር ሺህ ብር/፣ ለሎት 2/ሁለት/ 20,000 /ሀያ ሺህ ብር/፣ ለሎት 3/ሦስት/ 5000/አምስት ሺህ ብር/ እና ለሎት 4/አራት/ 2,000/ሁለት ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ የሚችሉ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ወልቂጤ ላይ ብር 300 /ሦስት መቶ/ ብቻ በመክፈል መግዛት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን የመጫረቻ ሰነዱን 01/አንድ/ ኦርጅናልና 02/ሁለት/ ፎቶ ኮፒ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት ወልቂጤ ከተማ ወደ አዲስ አበባ መውጫ G&P በስተምዕራብ 300 ሜትር ገባ ብሎ ከጉራጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አጠገብ በሚገኘው የውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር-23 ላይ ለዚህው ጉዳይ በተዘጋጀው የጨረታ ማስገቢያ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርብዎታል፡፡
የጨረታ ሰነድ ማስገቢያው በመጨረሻው የሥራ ቀን (በ15ኛዉ የሥራ ቀን) የጨረታ ሳጥኑ ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት ታሽጎ በዚያው እለት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ይከፈታል።
ማሳሰቢያ
- ተወዳዳሪዎች/ተጫራቾች ወይንም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው አለመገኘት የጨረታ መክፈቻ ቀኑን አይለውጥም፡፡
- ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ 011-3659083/0926251559/0916393987 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የውሃ፣ መስኖ እና ማዕድን ልማት ቢሮ
