Tender Detail

Tender Details

  • Company National Alcohol and Liquor Factory (ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ)
  • Address መካኒሳ ዋናው መስሪያ ቤት ፡ አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0711460279
  • Websitehttps://www.nalf.com.et/
  • Deadline01 Jan 2026, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price500.00
  • opening date2026-01-01 00:00:00
  • Categories Construction Works

ድርጅታችን በመካኒሳ የዋና መ/ቤት ህንፃ G+10 እና G+2 አጠቃላይ የህንፃ ጥገና አገልግሎት ግዥ በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡


የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 005/2018 ዓ.ም

ድርጅታችን በመካኒሳ የዋና መ/ቤት ህንፃ G+10 እና G+2 አጠቃላይ የህንፃ ጥገና አገልግሎት ግዥ በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች፡-

1. የታደሰ ፍቃድና የዘመኑ ግብር ለመከፈላችሁ መረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤

2. የማይመለስ ቫትን አካቶ በብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሠነዱን መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ገንዘብ ቤት ቢሮ ቁጥር 004 በመቅረብ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፤

3. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶቻቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነድ ኦርጅናል እና ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የሚቀርበው ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን አለመሆኑ በግልፅ መቀመጥ አለበት፡፡

4. ለጨረታ ዋስትና የሚሆን የሚያቀርቡትን አጠቃላይ ዋጋ 2% በሲፒኦለብቻው በኤንቨሎፕ በማሸግ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡

5. ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ሠነዶች ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሠዓት መካኒሳ በሚገኘው ዋናውመ/ቤት ግዥ ቢሮቁጥር 503ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዚያው ዕለት ከጠዋቱ 4፡10 ሠዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል::

6. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

ፓ.ሳ.ቁ 3516 011 869 0563 ፋክስ 011 869 0563

Addis Ababa, Ethiopia

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

Save Tender