ድርጅታችን ኬኬ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አቃቂ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የግንባታ ተረፈ ምርቶች፤ ያገለገለ የመኪና ዕቃዎች፤ የፋብሪካ ተረፈ ምርቶች እንዲሁም ሌሎች ንብረቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ኬኬ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ኬኬ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አቃቂ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የግንባታ ተረፈ ምርቶች፤ ያገለገለ የመኪና ዕቃዎች፤ የፋብሪካ ተረፈ ምርቶች እንዲሁም ሌሎች ንብረቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። በዚህም ጨረታ ላይ ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች ያለውን መስፈርት በማሟላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ያስታውቃል።
- ተጫራቾች ዘወትር በስራ ቀናት ከታህሳስ 01/2018 እስከ ታህሳስ 10/2018 ከጠዋቱ ከ2:30 እስከ 10፡00 ሰዓት ፋብሪካ በመሄድ ለጨረታ የወጡትን ንብረቶች መመልከት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በፋብሪካችን የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ከፍለው የጨረታ ዝርዝር ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ በቀረበው መስረት ለመወዳደር ላቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ የጨረታ ማስከበሪያ በሲፒኦ ገቢ ያደርጋሉ።
- የጨረታው ሳጥን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ታህሳስ 10/2018 ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ።
አድራሻ -- አቃቂ ቃሊቲ ከስቴድየም በታች ሰላም ህንፃ ፊት ለፊት ስልክ ቁጥር 0115 15 90 15
ኬኬ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ
