ድርጅታችን የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት በደቡብ ዲስትሪክት የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ ያወጣውን የጥራት መስፈርት የሚያሟሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ምርቶችን መስፈርቱን ከሚያሟሉ አምራቾች ወይም አቅራቢዎች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 01/2018
ድርጅታችን የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ ያወጣውን የጥራት መስፈርት የሚያሟሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ምርቶችን መስፈርቱን ከሚያሟሉ አምራቾች ወይም አቅራቢዎች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
1. ቆርቆሮ 35 ጌጅ 10. ባለቆብ ሚስማር 6ሳ.ሜ 19. የልብስ ሳሙና 250 ግራም
2. ቆርቆሮ 32 ጌጅ 11. ሩዝ ባለ 5 ኪ.ግ 20. የዱቄት ሳሙና ባለ 1 ኪ.ግ
3. ቆርቆሮ 30 ጌጅ 12. ሩዝ ባለ 10ኪ.ግ 21. የዱቄት ሳሙና ባለ 1*48*500ግ.ም ኪ.ግ
4. ሚስማር 6ሳ.ሜ 13. ሩዝ ባለ 25ኪ.ግ 22. የእቃ ማጠቢያ ሳሙና 1*100*100
5. ሚስማር 7ሳ.ሜ 14. አዮዲን ጨው ባለ 500ግ.ም 23. የእቃ ማጠቢያ ሳሙና 1*60*200
6. ሚስማር 8ሳ.ሜ 15. ፈሳሽ የምግብ ዘይት ባለ 5 ሊትር 24. ዳቦ ዱቄት ባለ 5ኪግ
7. ሚስማር 9ሳ.ሜ 16. ፈሳሽ የምግብ ዘይት ባለ 3 ሊትር 25. ዳቦ ዱቄት ባለ 10ኪግ
8. ሚስማር 10ሳ.ሜ 17. ፈሳሽ ሳሙና 5ሊትር 26. ፕሪንተር ወረቀት ደብል ኤ
9. ሚስማር 12ሳ.ሜ 18. ፈሳሽ ሳሙና 1ሊትር 27. ስንዴ
- ከተራ ቁጥር 1-10 እና ከተራ ቁጥር 14-25 ለተጠቀሱ ምርቶች አምራቾች ብቻ መካፈል የሚችሉ ሲሆን ከተራ ቁጥር 11-13,26,27 ለተጠቀሱ ምርቶች አምራቾች ወይም አቅራቢዎች መካፈል ይችላሉ።
- በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ ድርጅች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ፤ የንግድ ምዝገባ ፍቃድ ተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ፤ የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፊኬት፤ እና የግብር ክሊራንስ ያላቸው መሆን ይገባቸዋል
- ለጨረታ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 250.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ብር) ብቻ በመክፈል በሻሸመኔ ከተማ ቴሌ ፊት ለፊት በሚገኘው በደቡብ ዲስትሪክት ጽ/ቤት በመቅረብ ዘወትር በስራ ሰአት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡45-6፡30 እና ከሰኞ እስከ ዓርብ ከ7፡00-11፡00 መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና CPO ብቻ ለብቻው በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ማቅረብ ይጠበቅባቸውለ።
- የጨረታ መወዳደሪያ ዋጋ እና ከላይ ከተጠቀሱት ህጋዊ ሰነዶች በተለያየ የታሸገ ኤንቬሎፕ አንድ ኦሪጂናል እና አንድ ኮፒ በማድረግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር ተከታታይ 15 ቀናት ሆኖ ከ15ኛ ቀን ባለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ላይ ጨረታው ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሻሸመኔ ከተማ ቴሌ ፊት ለፊት በሚገኘው የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅ በደቡብ ዲስትሪክት ጽ/ቤት ቢሮ ባለው አዳራሽ ጨረታው ይከፈታል። ከጨረታ መዝጊያ ሰዓት በኋላ የሚቀርብ ሰነድ ተቀባይነት የለዉም።
- በመስፈርቱ ብቁ የሆነ ተጫራች ከአንድ በላይ ምርት መወዳደር ይችላል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር 251- 046 110 4518 ወይም
251-0462112322
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት በደቡብ ዲስትሪክት
