በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን የግዥና ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት በ2018 በጀት ዓመት የመኪና ኪራይ አገልግሎት ግዥዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ብሔራዊ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 004/2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን የግዥና ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት በ2018 በጀት ዓመት የመኪና ኪራይ አገልግሎት ግዥዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
1. ሎት 1 የፒክ አፕ መኪና፣ የሚኒባስ መኪና ኪራይ አገልግሎት ግዥ መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው፡
- ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤
- የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ/የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን ማቅረብ የሚችሉ፣
- ከገቢዎች የተወዳዳሪነት ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል፣
- የግብር መክፈያ መለያ ቁጥር/ Tin No / ያላቸው፣
- በመንግስት ግዥና የንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ ድረ-ገጽ WWW. PPA.gov.et)
- ተጫራቾች የሚያስዙት የጨረታ ማስከበሪያ/CPO/
ሀ. የፒክ-አፕ መኪና --------------- 20,000 ብር (ሃያ ሺህ ብር) CPO
ለ. የሚኒባስ መኪና ---------------- 20,000 ብር (ሃያ ሺህ ብር ብቻ) CPO
- ተጫራቾች በባንክ የተረጋገጠ በመ/ቤታችን ስም CPO ማስያዝ አለባችሁ ነገር ግን CPO ያላስያዘ ቢኖር ከጨረታ ውጪ ይሆናል፤
- ማንኛውም ተጫራች በጨረታው ለመወዳደር ጨረታው ከተዘጋጀ በኋላ የሚወዳደሩበት በተሰጠው በእስፔስፍኬሽን መሰረት መቅረብ አለበት፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች ከተራ ቁጥር 1 እስከ 7 የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ህጋዊ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ካወጣበት ጀምሮ 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ 15ኛ ፎቅ የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት በመቅረብና የማይመለስ 300 ብር /ሶስት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፣
- አሸናፊው ድርጅት ጥራቱን ያልጠበቀ ዕቃ ወይም አገልግሎት ካቀረበ በራሱ ወጪ የመለወጥ ግዴታ አለበት፣
- መ/ቤቱ ካቀረበው ሰነድ ውጪ በሌላ ሰነድ በአማራጭነት ማቅረብ አይቻልም፤
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ፋይናንሽል ኦርጅናል እና ኮፒ ደግሞ ቴክኒካል ኦርጅናል እና ኮፒ ዋጋ ሞልታችሁ በተናጠል ለየብቻ በፖስታ አድርጋችሁ የድርጅታችሁን ማህተምና ፈርማ የተወዳደራችሁበትን የሎት አይነት በፖስታው ላይ እየጻፋችሁ አስገቡ ካልጻፋችሁበት ደግሞ ፖስታችሁ እንደማይከፈት እያወቃችሁ የተባለበትን በሙሉ በማድረግ በግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ወደ ህንጻው ስትገቡ በቀኝ በኩል ባለው ሊፍት 15ኛ ፎቅ ፊት ለፊት ለጨረታ ተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባችሁ፤
- ጥቃቅንና አነስተኛ ተጫራቾች ለምትጫረቱባቸው ዕቃዎች (አገልግሎቶች የጨረታ ሰነዱን በነፃ ለመውሰድ
ሀ. ካደራጃችሁ መ/ቤት ደብዳቤ ማምጣት አለባችሁ፤
ለ. ሰነዱን በነፃ ለመውሰድ በመመሪያ መሰረት ለምታቀርቡት ዕቃ (አገልግሎቶች) አምራች መሆን አለባችሁ፤
- ተጫራቾች መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ዋጋ ላይ ስርዝ ድልዝ ሳይኖርባት በትክክል መሙላት አለባቸው::
- ጨረታው ከተከፈተ በኋላ አሸናፊው ድርጅት ባሸነፈበት ዕቃ ወይም አገልግሎት ላይ ውል ሲገባ የጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርበታል እንዲሁም አሸናፊ የሆነው ድርጅት አሸናፊነቱ እንደተገለፀለት ጨረታ ተከፍቶ ውጤት ከተለጠፈ ከ8 የሥራ ቀናት በኋላ በመቤታችን ቀርቦ ውል መግባት አለበት፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ጋዜጣው ከወጣበት ከ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ታሽጎ 3፡30 ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 11ኛ ቀን የበዓል ቀን ከሆነ ቀጣይ ባለው የሥራ ቀናት ውስጥ የሚከፈት ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
- ተጫራቾች የቀረበው ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆኑንና ያላካተተ መሆኑን መገለጽ አለባችሁ፡፡ ይህ ካልሆነ ግን መ/ቤቱ የቀረበውን ዋጋ ቫትን እንዳካተተ አድርጎ ይወስደዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ - አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን ክፍለ ከተማ አራዳ ወረዳ 1 ፒያሳ/ ስታስቲክስ ጎን እናት ህንጻ ፊት ለፊት ዋስትና ንግድ ማእከል 15ኛ ፎቅ ላይ ይገኛል ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-127-68-25 ይደውሉ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን
