ድርጅታችን ሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር የተለያዩ የደህንነት መጠበቂያ መገልገያዎችን ህጋዊ ፈቃድ ካላቸው አቅራቢዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ሐበሻ ሲሚንቶ
HABESHA CEMENT
የተለያዩ የደህንነት መጠበቂያ መገልገያዎችን ለመግዛት የወጣ ጨረታ
Procurement Ref. No. HCSC/EHS/002/2018
ድርጅታችን ሐበሻ ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር የተለያዩ የደህንነት መጠበቂያ መገልገያዎችን ህጋዊ ፈቃድ ካላቸው አቅራቢዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሟያሟሉ ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ በፖስታ አሽገው ግዢ እና አቅርቦት ክፍል እስከ ታኅሣሥ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን ጨረታው በዕለቱ 4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት መሆኑን እያሳወቅን፤ ተወዳዳሪዎች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ከላይ እስከተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ድረስ ብቻ ከታች በተመለከተው አድራሻ ማቅረብ የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
- ማንኛውም ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያለው እንዲሁም የዘመኑን ግብር የከፈለ ድርጅት በጨረታው መወዳደር የሚችል ሲሆን ተጫራቾች የፈቃዳቸውን ኮፒ እንዲሁም የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆቸው ከመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር አብረው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ዋጋ የሚያቀርቡባቸውን እቃዎች መጥቀስ/ማቅረብ ይኖርባቸዋል። በተጨማሪም ዋጋ ያቀረቡበትን የዕቃ አይነት በግልጽ መጻፍ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000 (መቶ ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይንም የባንክ ጋራንቲ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚቀርቡ የጨረታ ሰነዶችም ሆኑ ጨረታው ከተከፈተ በኋላ የሚደረጉ የማሻሻያ ጥያቄዎች ተቀባይነት የላቸውም።
- አሸናፊ ሆኖ የተመረጠ ተጫራች አሸናፊነቱ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ውል በመግባት ከ5 ባልበለጡ የስራ ቀናት ውስጥ ዕቃዎቹን ማቅረብ ይጠበቅበታል።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ከቫት ወይም ከማንኛውም የመንግስት ታክስ በፊት እንዲሁም ታክስን ጨምሮ መሆኑን በግልፅ ማመልከት ይኖርበታል። ይህ ባልሆነበት እና ዋጋ በግልፅ የማያቀርቡ ተጫራቾች ከጨረታው ሊሰረዙ ይችላሉ። ስርዝ ድልዝ የዋጋ ማቅረቢያ ተቀባይነት አይኖረውም።
- ሐበሻ ሲሚንቶ አ.ማ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን በተጨማሪም ለግዥ የቀረቡትን አቃዎች ዝርዝር ብዛት የመጨመርም የመቀነስም መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች ለግዥ የቀረቡትን የደህንነት መጠበቂያ እቃዎች ዝርዝር እንዲሁም ተጨማሪ መረጃዎችን ከዚህ በታች በተቀመጠው የድርጅቱ አድራሻ ማግኘት ይችላሉ።
አድራሻ፡ አሮጌው ቄራ ከንግድ ማተሚያ ቤት ጀርባ ጌት-አስ ኢንተርናሽናል ሕንፃ 7ኛ ፎቅ
ስልክ: 0944122311/0912850906
ሐበሻ ሲሚንቶ አ.ማ
