በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ስር የሚገኘው የነጌሌ ቦረና መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቅርንጫፍ ፅ/ቤት 45/አርባ አምስት/ እና ከዚያ በላይ ሰው መያዝ የሚችል አንድ (1) የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ለሠራተኞች ሰርቪስ አገልግሎት የሚሆን ለ1/አንድ/ ዓመት በኮንትራትአወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።
የሠራተኛ ሰርቪስ መኪና ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ስር የሚገኘው የነጌሌ ቦረና መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቅርንጫፍ ፅ/ቤት 45/አርባ አምስት/ እና ከዚያ በላይ ሰው መያዝ የሚችል አንድ (1) የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ለሠራተኞች ሰርቪስ አገልግሎት የሚሆን ለ1/አንድ/ ዓመት በኮንትራትአወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።
ከላይ በተገስፀው መሠረት ጨረታውን መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፦
- የ2018 ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያለው/ያላት
- የዘመኑን የስራ ግብር የከፈለ/የከፈለች።
- የተ.እ.ታ (ተ.ኦ.ታ) ተመዝጋቢ የሆነ/የሆነች እና የግብር መለያ ቁጥር ያለው/ያላት
- ኦርጅናል ሊብሬ ከነ ኮፒው ማቅረብ የሚችል/የምትችል
- የታደሰ የዓመቱን ቦሎ የለጠፈ እና 3ኛ ወገን ያለው/ያላት
- ጨረታውን ካሸነፈ በኋላ መኪናውን በማቅረብ በባለሙያ ለማስፈተሽ ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች
- የድርጅቱን ሠራተኞች ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ድረስ ባሉት የስራ ቀናት ውስጥ በመንግስት የሰራ ሠዓት መውጫና መግቢያ ሰርቪስ መስጠት በቀን 4 ምልልስ ይሆናል።
- የኪራይ ሁኔታ ለ1 (አንድ) ዓመት ነው።
- ከላይ የተጠቀሱትን ህጋዊ ማስረጃዎች ማቅረብ የሚችል /የምትችል/ ይህ ማስታወቂያ ከመጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ አስራ አምስት (15) ቀናት ጨረታው አየር ላይ የሚውል ስለሆነ መሳተፍ ይችላሉ።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በራሳቸሁ ህጋዊ የዋጋ ማቅረቢያ (ፕሪፎርማ) በመሙላት በታሸገ ፖስታ (ኢንቨሎፕ) አስከ ታህሳስ 23/2018 ዓ.ም 11 ሠዓት ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት ዶሎ በር ኬላ አጠገብ በሚገኘው መ/ቤታችን ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት አስተዳደር ክፍል ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን አውቃችሁ ታህሳስ 23/2018 ዓ.ም 11፡00 ሠዓት በኋላ ጨረታው ዝግ ተደርጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመግስቱ ማለትም ታህሳስ 24/ 2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 3:00 ይከፈታል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ፡- ከላይ የተዘረዘረሩትን ማስረጃዎች ማቅረብ የማይችሉ ተጫራቾች ዝቅተኛ የመጫረቻ ዋጋ
ቢያቀርቡም በጨረታው መመሪያ መሠረት አሸናፊ መሆን የማይችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ 0464451707 /0988080497 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
አድራሻ፡- የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ነጌሌ ቦረና ቅርንጫፍ ጎብቻ ቀበሌ ዶሎ በር ኬላ መውጫ።
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት
