የሚ/አ/ከ/አስ/ር ፋይናንስ ጽ/ቤት የሚ/አ/ከ/አስ/ር ትምህርት ጽ/ቤት በባለቤትነት ለሚያሰራው የውሽቅን 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ ስራ ለማሰራት ለደረጃ 5 እና ከዚያ በላይ ለሆኑ GC ተቋራጮችን በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የሚ/አ/ከ/አስ/ር ፋይናንስ ጽ/ቤት የሚ/አ/ከ/አስ/ር ትምህርት ጽ/ቤት በባለቤትነት ለሚያሰራው የውሽቅን 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ ስራ ለማሰራት ለደረጃ 5 እና ከዚያ በላይ ለሆኑ GC ተቋራጮችን በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ ተቋራጮች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት መወዳደር ይችላሉ
- ተጫራቾች በተሰማሩበት የሥራ መስክ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው
- በተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው
- ግብር ስለመክፈላቸው ከገቢዎች መ/ቤት ክሊራንስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- የጨረታ ሰነድ ከግዥ ንብ/አስ/ር የሥራ ሂደት ቢሮ በመቅረብ ሰነዱን 1000 /አንድ ሺህ ብር/ ከፍለው በመውሰድ መወዳደር ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነዱን ሞልተው ሲመልሱ ህጋዊነት ሰነድ እና ፋይናንሻል የተሞላበትን ሰነድ ኦርጅናልና 1 ኮፒ በአንድ እናት ፖስታ በማሸግ ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ማስከበሪያ 80,000 /ሰማንያ ሺህ ብር/ ከታወቀ ባንክ የሚሰጥ የተረጋገጠ ቼክ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና እና በባንክ የተረጋገጠ ሌተር አፍ ከሬዲት ለሚ/አ/ከ/አስ/ር ፋይናንስ ጽ/ቤት በማለት ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ሆኖ በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጎ በዚያው ቀን 4፡00 ላይ ሠዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሆኖ የሚታሸግበትም ሆነ የሚከፈትበት ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል።
- ሰነዱን ሞልተው ወደ ጨረታ ሳጥን ለማስገባት ሲመጡ ተመዝግበውና ፈርመው ማስገባት አለባቸው
- በጨረታ ማስታወቂያ ላይ የቃላት ወይም የትርጉም ስህተት ቢኖር በጨረታ ሠነዱ ላይ የተቀመጠው የበለጠ ተቀባይነት ይኖረዋል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ሚ/አ/ከ/አስ/ር ፋይናንስ ጽ/ቤት
