በደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ የኮንታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኮንታ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ለልዩ ልዩ የግንባታ ስራዎች ማስፈጸሚያ የሚውል ቆርቆሮ በ2018 በጀት ዓመት በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ለማግባት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ የኮንታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኮንታ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ለልዩ ልዩ የግንባታ ስራዎች ማስፈጸሚያ የሚውል ቆርቆሮ በ2018 በጀት ዓመት በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ለማግባት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሠረት ለመጫረት የምትፈልጉ፡-
- የዘመኑ በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ፤ 2/ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፤ 3/ በዘርፉ በመንግስት ግዥ ላይ የአቅራቢነት ሰርተፍኬት፤ 4/ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር)፤ 5/ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ምስክር ወረቀት፤ 6/ ከማንኛውም ግብርና ታክስ ዕዳ ነፃ ስለመሆኑ ከባለስልጣኑ መ/ቤት የግብርና የታክስ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችል፤ 7/ ከዚህ በፊት ያለውን የድርጅቱ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ከ2016 ዓ.ም ድረስ ያለውን ማቅረብ የሚችል፤ 10/ ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር) በCPO ከታወቀ ባንክ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፣
- ተጫራቾች የጨረታ ዶክመንት የማይመለስ 400 (አራት መቶ ብር) በመክፈል ከኮንታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 9 መውሰድ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ይህ ጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ እስከ 15ኛው ቀን ድረስ በኮንታ ዞን ፋይናንስና መምሪያ በመቅረብ የጨረታ ዶክመንቶች በመግዛትና በዋጋ ማቅረቢያ በመሙላት እያንዳንዱን ሎት ቴክኒካል ኦርጅናል 1 እና ኮፒ 1 ፋይናንሻል ኦርጅናል 1 እና ኮፒ 1 በድምሩ 4 ፖስታ የድርጅታችሁን ማህተም በማድረግ በአንድ እናት የጨረታ ፖስታ በማሸግ በኮንታ ዞን ፋይናንስና መምሪያ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሣጥን የሚከፈተው በ15ኛው ቀን ሲሆን ይህ ቀን የመንግሥት ሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ታሸጎ በዚሁ ዕለት በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮንታ ዞን ፋይናንስና መምሪያ ይከፈታል፡፡
- በጨረታ ማስታወቂያ ያልተገለጹ ሌሎች የመወዳደሪያ ነጥቦች (መስፈርቶች) በጨረታ ዶክመንቱ መሠረት ተግባራዊ ይደረጋል፡፡
- የሂሳብ ስህተት ከጠቅላላ ድምር ከፍታ እና ዝቅታ 5% በመመሪያው መሠረት ተግባራዊ ይሆናል፡፡
- በጨረታ ማስታወቂያ እና ዶክመንቱ ላይ የተገለፁትን የመወዳደሪያ ነጥቦችን ያሟላ ተጫራች ብቻ ወደ ድህረ ግምገማ ያልፋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- በቢሮ ስልክ ቁጥር 0917388691/0935138008 አድራሻችን- በደ/ም/ህ/ክ/መ/ኮንታ ዞን ፋይናንስ መመሪያ ከጅማ ከተማ በስተደቡብ 102 ኪሜ ርቀት ላይ በአመያ ከተማ ይገኛል፡፡
በደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ የኮንታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኮንታ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት
