በምሥራቅ ጐጃም ዞን የብቸና ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በ2018 በጀት ዓመት ከሐምሌ 1/2012 እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ/ም የ6 ዓመት ኦዲት ማስደረግና ያገለገሉ ዕቃዎችን ሽያጭ ማከናወን ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ኦዲት ማስደረግና ያገለገሉ ዕቃዎች ሽያጭ
በምሥራቅ ጐጃም ዞን የብቸና ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በ2018 በጀት ዓመት ከሐምሌ 1/2012 እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ/ም የ6 ዓመት ኦዲት ማስደረግና ያገለገሉ ዕቃዎችን ሽያጭ ማከናወን ይፈልጋል።
ስለሆነም፡-
ሎት1፣ የ6 ዓመት ኦዲት ማስደረግ / ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ ጨረታ /
ሎት 2፣ የተለያዩ Kw ፖንፖዎች እስከ ገመዳቸው ሞተሩን ጨምሮ የተለያዩ Kw ዲናሞዎች ጀኔሬተር USA 135KW ቁርጥራጭ ብረቶች፣ PVCዎች፣ HDPE ቧንቧዎች፣ ያገለገሉ የውሃ ቆጣሪዎች ሽያጭ
ተጫራቾች፡-
- የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ያላቸው፤
- ድርጅቱን ኦዲት ለማድረግ የሚያስችል የኦዲተርነት ሙያ ፈቃድ ያለው፣
- ተጫራቾች ከላይ ከተዘረዘሩት ከ1-3/ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከኦርጅናል ሰነዱ ጋር አያይዘው ቢሮ ቁጥር 10 በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 2% በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ሆኖም ጨረታው ተከፍቶ አሸናፊው ከተለየ ከ5 ቀን በኋላ ተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙትን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚመለስ ይሆናል ይሆናል።
- የጨረታ አሸናፊ ማሸነፉ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ በማስያዝ ውል መያዝ ይጠበቅበታል።
- የጨረታ አሸናፊው ማሸነፉ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ተገቢውን የውል ማስከበሪያ ያልያዘና ውል ያልፈፀመ እንደሆነ ድርጅቱ ያስያዙትን የጨረታ ማስከበሪያ መውረስ ይችላል።
- ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን በ16ኛው ቀን 3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውበተገኙበት ይከፈታል። ሆኖም ተጫራቾች ወይም ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት መ/ቤቱ ጨረታውን ይከፍታል። ይህ ቀን የበዓላት ቀን ከሆነ በተመሣሣይ በሥራ ቀን ይከፈታል።
- የአገለገሉ ዕቃዎች አሸናፊው ግለሰብ ወይም ድርጅት ድርጅቱ ድረስ በመምጣት በራሱ ወጪ ዕቃዎችን ማንሣት ይኖርበታል።
- ያገለገሉ ዕቃዎች ሽያጭ ላይ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት መወዳዳር ይችላል። ለሽያጭ የሚቀርቡት ያገለገሉ ዕቃዎች አይነትና ዝርዝር ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሠነዱ ያገኛሉ በተጨማሪም ድርጅቱ አጥር ግቢ በመገኘት በአካል ማየት ይችላሉ።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስ.ቁ 0586650376/ 0924322937 መደወሉ ይችላሉ።
በምሥራቅ ጐጃም ዞን የብቸና ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት
