በደ/ም/ኢ/ሕ/ክ/መንግስት ግብርና ቢሮ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም /FSRP/ Credit no IDA-71560 በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ በሎት አከፋፍሎ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ም/ኢ/ሕ/ክ/መንግስት ግብርና ቢሮ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም /FSRP/ Credit no IDA-71560 በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ በሎት አከፋፍሎ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሰረት፡-
- ሎት 01 የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ ዓይነቶች መለያ ቁጥር FT-SWEPR-515012-GO-RF Q
- ሎት 02 ሞተር ሳይክል መለያ ቁጥር ET-SWEPR-515056-GO-REQ
- ሎት 03 የእንስሳት ጤና ክሊኒክ ቁሳቁሶች የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ የንብ ማነቢያ ቁሳቁሶች መለያ ቁጥር ET-SWEPR-515066-GO-RFQ
- ሎት 04 ጉልበት ቆጣቢ ቴክኖሎጂ መለያ ቁጥር ET-SWEPR-515044-GO-REQ
- ሎት 05 ሂልየም ጋዝ ET-SWEPR-515066-GO-RFQ
- ሎት 06 የግብርና ኖራ ET-SWEPR-499060-GO-REQ
በዚሁ መሠረት በጨረታው መሳተፍ የሚትፈልት ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የማሟላት ግዴታ አለባቸው።
- ቀጥታ ግንኙነትና አግባብነት ያላቸው የ2018 ዓ.ም የንግድ ፍቃድ ያሳደሱ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸው የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (Tin number) VAT /የተጨማሪ እሴት ታክስ/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያሳይ የምስክር ወረቀት ኮፒ ማቅረብ የሚችሉ እና የ2017 በጀት ዓ/ም ግብር ስለመክፈላቸው ክሊራንስ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
- ለሎት 03 ተጫራቾች የእንስሳት መድሃኒትና የህክምና መሳሪያዎች ከግብርና ባለስልጣን የተሰጠ የታደሰ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ እና የእንስሳት መድሃኒትና የህክምና መሳሪያዎች አስመጪ ወይም ጅምላ አከፋፋይ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር ለሎት 01 እና ሎት 02 ለእያንዳንዳቸው 20,000 /ሃያ ሺህ ብር / እና ለሎት 03፣ 04 ፣ 5 እና ሎት 06 ለእያንዳንዳቸው 15,000 /አስራ አምስት ሺህ ብር/ ህጋዊ ከሆነው ባንክ የተረጋገጠ C.P.O ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ቢድ ቦንድ ማስያዝ የሚችሉ (Unconditional bid bond)
- ተጫራቾች የጨረታ መወዳደሪያ ሰነድ ግዥ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ) ብር ከሎት 01-06 ድረስ ለተዘረዘሩት ግዥዎች በደ/ም/ኢ/ሕ/ክ/መንግስት ግብርና ቢሮ ስም በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000454620918 ላይ ገቢ በማድረግ የባንክ አድቫይስ እና የታደሰ ንግድ ፍቃድ ኮፒ በመያዝ ግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 4 በመገኘት ዘወትር ይህ ጨረታ ማስታወቂያ በአየር ከዋለበት ቀን ጀምሮ ተከታታይ 30 ቀናት ውስጥ የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ይህ ማስታወቂያ በግልጽ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ30 /ሰላሳ/ ተከታታይ ቀናት አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ኦርጅናል እና 1 /አንድ/ ኮፒ ለየብቻ በመለየት ፊርማና የድርጅቱን ማህተም በማሳረፍ በደ/ም/አ/ሕ/ክ/መንግስት ግብርና ቢሮ ግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 4 ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
- ጨረታው በ31ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ታሽጎ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል።
- 31ኛው ቀን የመንግስት የስራ ቀን ሆኖ ካልተገኘ በሚቀጥለው የመንግስት የስራ ቀን ጨረታው በተመሳሳይ ቀንና ሠዓት ታሽጎ ይከፈታል፡፡
- የጨረታ አሸናፊ የሆነው አቅራቢ ዕቃዎችን በተፈለገው ጊዜ በራሱ ወጪ ቦንጋ በሚገኘው ደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ/ ግብርና ቢሮ ቦንጋ ከተማ በማድረስ ስለትክክለኛነቱ በማረጋገጥ ማስረከብ አለበት።
- ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 10% ለማስያዝ ፍቃደኛ መሆን አለባቸዉ።
- ተጫራቾች ሁሉንም ዕቃ ዋጋ በክፍል 4 በቀረበው የዋጋ ማቅረቢያና ስፔስፊኬሽን ቅጽ ላይ ከነቫት ሞልተው ማቅረብ አለባቸው፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0473311723 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
ደ/ም/ኢ/ሕ/ክ/መንግስት ግብርና ቢሮ
