የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የቆሻሻ ውሃ ፍሳሽ ማስወገጃ ፕሮጀክት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት አስፈልጓል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የቆሻሻ ውሃ ፍሳሽ ማስወገጃ ፕሮጀክት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት አስፈልጓል፡፡
|
ተ/ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
|
1 |
በአባ ሳሙኤል የሚገኘው ማረ/ቤት የቆሻሻ ውሃ ፍሳሽ ማስወገጃ መስመር ዝርጋታ ስራ |
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቶች ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባችሁ፡፡
- በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው መሆን በዘርፉ የተሰማሩ ለመሆናቸው በጀርባው የተገለጸ መሆን አለበት፡፡
- የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉ፡፡
- ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ፣ የታደሰ የዘመኑ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉና የታደሰ የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የመንግስት መ/ቤቶች ለሚያወጡት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የአቅራቢዎች የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው እንዲሁም በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ከገቢዎች ጉምሩክ ባለስልጣን የዘመኑ ግብር ከፍለው ስለማጠናቀቃቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- አማራጭ ዋጋ በዚህ ጨረታ ማቅረብ አይቻልም፡፡
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታ ውጤቱ እንደታወቀ ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ተብሎ በተዘጋጀው ከባንክ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.ኦ 100,000 ብር ማስያዝ ይኖርባቸኋል፡፡ እንዲሁም የባንክ ዋስትና የሚያስይዙ ተጫራቾች የቆይታ ጊዜው ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምር የሚቆጠር 90 ቀንና ከዚያ በላይ መሆን ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነዶችና የዋጋ ማቅረቢያዎችን /ፋይናንሻል/ ሰነዶችን በተለያዩ ፖስታ ታሽጎ ለየብቻ መቅረብ አለበት ቴክኒካልና ፋይናንሻል ሰነድ በአንድ ላይ አሽጎ ያቀረበ ተወዳዳሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከጨረታው ውጭ ይደረጋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች የሚያስገባው ሰነድ ፋይናንሻል ለና ቴክኒካል የጨረታ ሰነድ አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ በተለያዩ ፖስታ በሰም በማሸግ በፖስታው ላይ የጨረታ ሰነዱን ቁጥር የሚጫረትበትን በትክክል መጻፍ እንዲሁም በፖስታው ላይ እና በሁሉም የመጫረቻ ሰነድ ላይ የድርጅቱን ማህተም በመምታት ማስገባት ያለበት ሲሆን ስርዝ ድልዝ፣ በፍሉድ የጠፋ እና ዋጋ ያልተሞላበት ዝርዝር ተቀባይነት የለውም፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚያሲዙት ሲ.ፒ.ኦ ከቴክኒካል ሰነዶች ጋር በአንድ ላይ ታሽገው መቀረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ፒያሳ አ/አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኪሚሽን ከፍ ብሎ በሚገኘው ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ዋናው መ/ቤት 1ኛ ፎቅ የፋይናንስ ቢሮ ቀርበው በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ጥር 28/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 6፡00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን በመ/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ዘግይተው የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም፣
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በከፊልም ሆነ ሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫቾች የሚወዳደሩባቸውን ዕቃዎች ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ፡-
በስልክ ቁጥር 01-11-26-56-65 ደውስው መጠየቅ ይችላሉ።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን
