ኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወቸ አክሲዮን ማህበር በአሉት ሁለት ህንፃዎች በጨረታ አወዳድሮ የኮሪዶር መብራት አምፖል ዙሪያውን ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የሁለቱንም ሕንፃ ዙሪያ የኮሪዶር መብራት አምፖል ማሰራት
ኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወቸ አክሲዮን ማህበር በአሉት ሁለት ህንፃዎች በጨረታ አወዳድሮ የኮሪዶር መብራት አምፖል ዙሪያውን ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተቀመጠው የኮሪዶር ልማት የህንፃ መብራት በየሁለት ሜትር ርቀት የሕንጻዎቹ የውጭ ገጽታ ከላይ በተጠቀሰው ርቀት ማሰራትና አክሲዮን ማህበሩ አስፈላጊ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች አቅርቦ ሌሎች መሳሪያዎችንና የሕንጻ መወጣጫዎች በራሳቸው አሟልተው የሚሰሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት።
ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች፡-
1. በዘርፋ 2018ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ እና የንግድ ምዝገባ ሰርተፊኬት፣
2. የቫት እና የግብር ከፋይነት ሰርቲፈኬት (TIN Number)
3. ለሚከፈለው ክፍያ ህጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ የሚችል
4. ቢያንስ በተመሳሳይ ሥራ የስራ ልምድ ማቅረብ የሚችል
5. ማንኛውም ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ 10,000 ባንክ ሲፒኦ (CPO) አሰርቶ በማህበሩ ስም ማስያዝ የሚችል
6. ከላይ የተጠቀሱትን ሁኔታዎች የሚያሟሉ የስራ ተቋራጮች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 5 (በአምስት) ቀናት የጨረታ ሰነድ ከአክሲዮን ማህበሩ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት የሚችሉ ሲሆን የሞሉትን የመጫረቻ ዋጋቸውንና አስፈላጊ ሰነዶችን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስገባት ትችላላችሁ፡፡
7. ጨረታው ከወጣበት ቀን አምስተኛው ቀን 8፡00 ሰአት ተዘግቶ በዛው ቀን 9፡00 ሰአት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአክሲዮን ማህበሩ ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡
8. የጨረታው አሸናፊ በማስታወቂያ ከተገለፀ በ2 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ አክሲዮን ማህበሩ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ ውል መዋዋል ይጠበቅበታል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ስራውን በራሱ ፈቃድ እንደተወ ተቆጥሮ ያስያዘውን የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ (CPO) ለማህበሩ ገቢ ይደረጋል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
· ማህበሩ የተሻለ አመራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፈልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
· አድራሻች:- በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው አጠና ተራ ከቴሌው ጀርባ ባለው የአ/ማህበሩ የገበያ ማዕከል ሕንጻ ቁጥር 2 አራተኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 4
· ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 09-12-05-47-92 /09-32-08-03-77
ኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክስዮን ማኅበር
