በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕፃናትና ቤተሰብ ጉዳይ ድርጅት የገነተ ኢየሱስ ሕፃናትና ቤተሰብ ልማት ፕሮግራም ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ለትምህርት ቤት የሚሰጥ የተለያየ ዓይነትና መጠን ያለው ለስፖርት አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶችን አጫርቶ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕፃናትና ቤተሰብ ጉዳይ ድርጅት የገነተ ኢየሱስ ሕፃናትና ቤተሰብ ልማት ፕሮግራም ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ለትምህርት ቤት የሚሰጥ የተለያየ ዓይነትና መጠን ያለው ለስፖርት አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶችን አጫርቶ ለመግዛት ይፈልጋል።
1. በጨረታው ለመወዳደር የሚያበቃቸው በሥራ ዘርፉ ፈቃድ ያላቸውና የታደሰ የዘመኑ ንግድ ሥራ ፈቃድ መኖር አለበት
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት መቅረብ አለበት
3. በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት መኖር አለበት
4. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 400.00 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል ከድርጅታችን መውሰድ ይኖርባቸዋል።
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ቡድ ቦንድ 2% በባንክ የክፍያ ትዕዛዝ CPO ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለሰባት 17/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
7. ጨረታውን አሸናፊ ድርጅት ለትምህርት ቤቱ የሚሰጥ ለስፖርት አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶች ውል ከተፈራረመበት ዕለት ጀምሮ በ5 /አምስት/ ቀናት ውስጥ ማስረከብ ይኖርበታል። እንዲሁም በራሱ ትራንስፖርት ማስተባበሪያ ጽ/ቤታችን ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል።
8. ለስፖርት አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶች ብዛት በሚሰጠው ዋጋ መሠረት ሊጨምርም ሊቀንስም ይችላል።
9. ጨረታው ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም 6፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ ከሰዓት በኋላ 8፡00 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
10. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
11. ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011-1-14-29-48 መጠየቅ ይቻላል።
12. CPO የሚሠራበት ስም EOC - CFAO Genete Eyesus Child and Family Development Program Coordination Office በሚል ይሆናል።
አድራሻ
በየካ ክ/ከ ወረዳ 1 ከገነተ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ዝቅ ብሎ ወደ ፈረንሣይ ኤምባሲ በሚወስደው መንገድ ሚያዚያ 23 ት/ቤት ሳይደርሱ ከሚገኘው ማስተባበሪያ ጽ/ቤታችን በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕፃናትና ቤተሰብ ጉዳይ ድርጅት
