Tender Detail

Tender Details


የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት በዋናው መስሪያ ቤት የሚገኘውን ነባሩ ህንፃ የቢሮ ውስጥ የእድሳት ስራዎችና ተዛማጅ የሆኑ የተለያዩ ስራዎችን ለማሰራት የኢንትሪዬር ዲዛይን፣ የኔትወርክ ዲዛይንና ገመድ ዝርጋታ፣ የግንባታ ማጠናቀቀ ስራ እና የቢሮ ሙሉ ዕቃ የዲዛይንና የገጠማ ስራዎች /Interior Design, Finishing Construction Work, Network Design and


ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ኢሎአ/006/2018

 

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት 2018 በጀት ዓመት በዋናው መስሪያ ቤት የሚገኘውን ነባሩ ህንፃ የቢሮ ውስጥ የእድሳት ስራዎችና ተዛማጅ የሆኑ የተለያዩ ስራዎችን ለማሰራት የኢንትሪዬር ዲዛይን፣ የኔትወርክ ዲዛይንና ገመድ ዝርጋታ፣ የግንባታ ማጠናቀቀ ስራ እና የቢሮ ሙሉ ዕቃ የዲዛይንና የገጠማ ስራዎች /Interior Design, Finishing Construction Work, Network Design and Cable Installation Work and Furnish Office Materials/ ላይ በዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ስራዎችን ማሰራት ይፈልጋል።

ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች ሁሉ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 27 ቀን 2018 . ከጠዋቱ 400 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ስራ የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ስም በተከፈተ የባንክ ሒሳብ ቁጥር ገቢ በማድረግ ዋናውን ማስረጃ በማቅረብ የጨረታ ሰነዱን በመግዛት በጨረታው መወዳደር ይችላሉ፣ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማስያዝ ያለባቸው ብር 250,000.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) በሲ.. /C.PO/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ /Irrevocable or unconditional Bank Guarantee from Recognized Bank of Ethiopia/ ማስያዝ አለባቸው።

ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ውስጥ የተገለፁትን የቴክኒካል ሰነዶችን የያዘ አንድ ዋናና አንድ ቅጂ ለየብቻው እንዲሁም የፋይናንሻል ሰነድ የያዘ አንድ ዋናና አንድ ቅጂ ለየብቻው እና የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናውን ለየብቻው በፖስታ በማሸግ ሁሉንም በአንድ ትልቅ ፖስታ በማድረግ እስከ ጥር 27 ቀን 2018 . ከጠዋቱ 400 በዓት ድረስ ብቻ ለዚሁ ስራ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ አለባቸው።

ጨረታው ጥር 27 ቀን 2018 . ከጠዋቱ 400 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ጥር 27 ቀን 2018 . ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዋና /ቤት ይከፈታል። አገልግሎቱ ስለጨረታው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-011-126-78-16 ደውሎ መረዳት ይቻላል።

 

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት

Save Tender