በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በጌዴኦ ዞን የወናጎ ወረዳ ሳይናንስ ጽ/ቤት ከጤና ጽ/ቤት በቀረበው ጥያቄ መሰረት በ2018 በጀት ዓመት በጀምጀም ቀበሌ እና በጦቅቻ ቀበሌ ጤና ኬላ ግንባታ ማሰራት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 002/2018
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በጌዴኦ ዞን የወናጎ ወረዳ ሳይናንስ ጽ/ቤት ከጤና ጽ/ቤት በቀረበው ጥያቄ መሰረት በ2018 በጀት ዓመት በጀምጀም ቀበሌ እና በጦቅቻ ቀበሌ ጤና ኬላ ግንባታ ማሰራት ይፈልጋል።
በመሆኑም መ/ቤቱ የሚሰራቸው ዝርዝር የያዘ ሰነድ በሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ተወዳዳሪዎች የሚከተሉትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾችን ይጋብዛል።
· በዘርፉ ሕጋዊ የግንባታ ሥራ ፍቃድ ያላቸው
· የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው
· የዘመኑን ግብር የከፈለ ከመንግስት ዕዳ ነጻ የሆነ
· ከኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ወይም አግባብነት ካለው
· የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ ያለው
· የ VAT ተመዝጋብ የሆኑ
· በግንባታ ሥራ ደረጃ BC/ GC 7 እና ከዚያ በላይ የሆኑ
· የግብር ከፋይነቱ መለያ ቁጥር ያለ /TIN NO/
· በአቅራቢነት የተመዘገበ
· አሸናፊ ድርጅት መክፈል ያለበትን የሽያጭ ታክስ 3% ይከፍላል
· አሸናፊ ድርጀት የውል ማከበሪያ ያሸነፈበትን ግንዛበ ልክ 10% ያስይዛል
· ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የግንባታ ጨረታ ሰነድ የፋይናንስ ግዥ ን/አ/ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 10 በመቅረብ የማይመለስ ብር 200 ብር (ሁለት መቶ ብር) ብቻ በመግዛት መወዳደር ይችላሉ።
· ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን እና ሌሎች ተፈላጊ መረጃዎችን ማለትም ፋይናንሻል ኦርጅናል በአንድ ፖስታ ቴክኒካል ኦርጅናል በአንድ ፖስታ በማሸግ እንዲሁም ፋይናንሻል ኮፒ እና ቴክኒካል ኮፒ ለብቻ ታሽጎ በእናት ፖስታ በማድረግ ማቅረብ አለባቸው።
· ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት የጨረታ ማስከበሪያ /CPO/ ብር 10,000 (አስር ሺ ብር) ማስያዝ ያለበት ሲሆን CPO ለብቻው ታሽጎ ኦርጅናል ቴክኒካል ዶክመንት ጋር መቅረብ አለበት።
· ጥሬ ገንዘብ ማቅረብ የለባቸውም።
· የሥራ ተቋራጮች የጨረታ ሰነዱን ሊገዙ ሲመጡ የግንባታ ሳይቱን አይተው ማረጋገጥ አለባቸው።
· ጨረታው የሚከፈተው ይህ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ የሥራ ቀናት አየር ላይ ቆይተው በ22ኛው ቀን የሚከፈት ሲሆን ዕለቱ በዓል ወይም ቅዳሜና ዕሁድ ከሆነ በቀጣዩ ሥራ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወ/ወ/ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በመሰብሰቢያ አዳራሽ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በ4፡30 ሰዓት ይከፈታል።
· ማንኛውም ተጫራች አንዱ ባቀረበው ዋጋ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም።
ማሳሰቢያ፡- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በጌዴኦ ዞን የወናጎ ወረዳ ፋይናንስ
ጽ/ቤት
