በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል የአቮካዶ እና የማንጎ ማውረጃ (Avocado and mango fruit picker technology) ብዛት 350 (ሶስት መቶ ሃምሳ) ቴክኖሎጂ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የብዜት ሥራ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ግ.ጨ. 04/2018
በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል የአቮካዶ እና የማንጎ ማውረጃ (Avocado and mango fruit picker technology) ብዛት 350 (ሶስት መቶ ሃምሳ) ቴክኖሎጂ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የብዜት ሥራ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች ከተራ ቁጥር ከ1-6 የተዘረዘሩ መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
1. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ።
2. የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
3. የዘመኑን የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድና የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
4. በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ ስለመሆናቸው ከሊራንስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
5. በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢዎች ዝርዝር ላይ የተመዘገቡ ስለመሆናቸው የምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
6. ከዚህ በፊት በመልከሳ ግብርና ምርምር ማዕከል የግብርና ምህንድስና ምርምር ዘርፍ ወይም በተመሳሳይ በሌሎች ማዕከላት በሚገኙ የግብርና ሜካናይዜሽን ምርምር ዘርፍ ውስጥ የሰለጠኑ፣ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣ ተቀባይነት ያለው የማምረቻ ጥሬ ዕቃን ለመጠቀምና ተጠቃሚ አርሶ አደሮችን ለከፍተኛ ወጪ እንደማይዳርግ ማስተማመኛ በመስጠት የብዜት ቴክኖሎጂ ሽግግር ውል ለመፈረም ፍቃደኛ የሆኑ፣ ቴክኖሎጂዎችን የማምረት ልምድ ያላቸው (Success story) እንዲሁም የማምረቻ ማሽኖች ያላቸውና በአካል ማሳያት የሚችሉ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማባዛት አቅዷል፡፡ ተጫራቾች የቴክኖሎጂዎችን ናሙና ማዕከል ድረስ በአካል በመምጣት እና በማየት መተማመኛ መስጠት ይጠበቅባቸዋል። ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ20 (ሃያ ቀን) ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ ከ2፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት እና ከሰዓት በኋላ ከ7፡00 ሰዓት እስከ 10፡30 ሰዓት ድረስ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ 5,000.00 /አምስት ሺህ ብር/ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ የተመሰከረ CPO በማስያዝ ከአዳማ ወደ አሰላ በሚወስደው መንገድ 17 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኘው በመልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል የግዥና ፋይናንስ ስራ አስፈጻሚ የማይመለስ ብር 800 (ስምንት መቶ) በመክፈል የተዘጋጀውን ሰነድ በመግዛትና በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ የመወዳደሪያ ሰነዳችሁን ግ.ጨ. 04/2018 የመጫረቻ ሰነድ ተብሎ በሕግና በደንቡ መሠረት ታሽጎ መግባት ይኖርበታል፡፡ ጨረታው ለ20 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ በ20ኛው ቀን ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ታሽጎ በዛው እለት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማዕከሉ የስብሰባ አዳራሽ በግልፅ ይከፈታል፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት እለት የበዓላት ቀን ወይም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ የጨረታው መክፈቻ ቀን ወደሚቀጥለው የሥራ ቀን ይዘዋወራል። ዘግይተው የሚመጡ የመጫረቻ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም፡፡
ማዕከሉ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ አሸናፊ የሚሆነው ድርጅት ወይም ግለሰብ ላሸነፉባቸው የቴክኖሎጂ ብዜቶች በራሳቸው ወጪ ማዕከሉ ድረስ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
ለተጨማሪ መረጃ
+251983755061 ወይም
+251 911942650 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል
መልካሣ
