በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ለምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ኘሮግራም የበጀት ድጋፍ የዶሮ ጫጩት ማስፈልፈያ ማሽን ግዥ በግልጽ ጨረታ ከዚህ በታች በሰንጠረዥ በተዘረዘረው መሠረት በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የዶሮ ጫጩት ማስፈልፈያ
ማሽን ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ 213/18
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ለምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ኘሮግራም የበጀት ድጋፍ የዶሮ ጫጩት ማስፈልፈያ ማሽን ግዥ በግልጽ ጨረታ ከዚህ በታች በሰንጠረዥ በተዘረዘረው መሠረት በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የዕቃው አይነት |
መለኪያ |
ብዛት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
የሚታሸግበት ሰዓት |
ሰነዱ የሚገኝበት ቦታ |
|
1 |
የዶሮ ጫጩት ማስፈልፈያ ማሽን |
በቁጥር |
2 |
300,000 |
በ31ኛው ቀን በ4፡00 ታሽጎ በዕለቱ 4:10 ሰዓት ይከፈታል |
ደ/ኢ/ግ/ቢሮ ዲላ መምህራን ኮሌጅ ግቢ |
በንግድ ስራ ዘርፉ የታደሰ ፍቃድ የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸውና የቫት መዝጋቢነት ማስረጃዎች ያላቸውና የሚያቀርቡ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
· ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ለ60 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል።
· በተጫራቾች የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ሲ/ፒ/ኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ያሲያዙበትን ማቅረብ አለባቸው
· ተጫራቾች በቢሮ የተዘጋጀውን መደበኛ የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ቀናት እስከ 30ኛ ቀን 11፡30 ድረስ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል በዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ መምህራን ኮሌጅ ግቢ ወስጥ ከሚገኘው የግብርና ቢሮ ግዥ ንብ/አስ/ዳይሬከቶሬት ከፍል መውሰድ ይችላሉ።
· ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ በመሙላት ቴክኒካል ሰነድ አንድ ኦርጂናል እና አንድ ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሽያል ሰነድ አንድ ኦርጂናል እና አንድ ኮፒ አዘጋጅቶ በማሸግና ሁሉንም በአንድ እናት ፖስታ ከቶ በማሸግ በ31ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት በቢሮው ግዥ ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይቻላል። እንዲሁም የጨረታው ሳጥን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ 4፡10 ተጫራቾች (ተወካዮቻቸው) በተገኙበት በቢሮው የግዥ ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ክፍል ይከፈታል።
· ቢሮው በቀረበው ጨረታ ላይ ካሸናፊው ድርጅት ጋር ውል ከመፈራረሙ በፊት የግዥውን 20% ፐርሰንት መቀነስ ወይም መጨመር ይችላል።
· የጨረታው መክፈቻ ቀን ማለትም 31ኛው ቀን የመንግሥት የሥራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በቀጣይ ባለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓትና ቦታ የሚከፈት ይሆናል።
· ከአንድ በላይ የሆኑ ተወዳዳሪዎች ያቀረቡት ዋጋ እኩል በሚሆንበት ወቅት በእጣ የሚለይ ይሆናል።
· ቢሮው ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ 046-131-0134 ይጠቀሙ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት ግብርና ቢሮ
