Tender Detail

Tender Details

  • Company በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
  • Address በስልጤ ዞን ከአዲስ አበባ ርቀቱ 221 ኪ.ሜ ሲሆን 176 ኪ.ሜ አስፋልት እና 45 ካ.ሜ ፒስታ መንገድ ነው ፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 251912288101
  • Website
  • Deadline17 Feb 2026, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price500.00
  • opening date2026-02-17 00:00:00
  • Categories Construction Works

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ለቀልጦ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ኮሚኒቲ ፋርማሲ ብቁ ተጫራቾችን በጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል።


በድጋሚ የወጣ የግንባታ የጨረታ ማስታወቂያ

 

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ፋይናንስ /ቤት ለቀልጦ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ኮሚኒቲ ፋርማሲ ብቁ ተጫራቾችን በጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታው ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ይህ ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ስለግንባታው የሚገልጽ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመከፈል በምስ/አዘ/በር/ወረዳ ፋይናንስ /ቤት ቢሮ ቁጥር 10 ድረስ በመምጣት ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት የጨረታ ሰነድ መግዛት ትችላላችሁ።

በዚህ ጨረታ መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች GC/BC-6 እና ከዛ በላይ የሆኑ

1.     ተጫራቾች በዘርፉ ያላቸው የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ ከግብር ሰብሳቢ /ቤት የተሰጠ መቅታዊ የግብር ክፍያ ማረጋገጫ፣ የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ በአቅራቢዎች ስም ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸው የሚገልጽ ማስረጃና ሌሎች ሰነዶችን ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።

2.     ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 80,000 (ሰማንያ ሺህ) ብር በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ወይም CPO ምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ፋይናንስ /ቤት ስም አሰርተው ለዚህ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በታሸገ ፖስታ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል የጨረታ ሰነድ ማስገባት አለባቸው። ዘግይቶ የሚቀርብ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡

3.     ተጫራቾች ኒካል እና ፋይናንሻል የመጫረቻ ሰነዶችን ለእያንዳቸው አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ የጨረታ ሰነድ ለየብቻ በታሸገ ፖስታ ህጋዊ ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው።

4.     ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በጨረታ ሰነድ ላይ በመሙላት ዋናውንና ኮፒውን በሰም በታሽገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ለዚህ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

5.     ጨረታው 15ኛው ቀን 8:00 ሰዓት ታሽጎ በዛው ቀን ከቀኑ 830 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሠው አድራሻ ይከፈታል።

6.     የግንባታው ሳይት (ቦታ) በምስ/አዘ//ወረዳ በቂልጦ 01 ውስጥ ነው

7.     በተጫራቾች ተሞልተው የሚቀርቡ ፋይናንሻል ዋጋዎች እና የግንባታ ስራው ቴክኒካል የመወዳደሪያ ሀሳብ ደጋፊ ሰነዶች በግልጽና በጥራት የሚታዩና ስርዝ ወይም ድልዝ ያልሆኑ መሆን አለባቸው

8.     መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

9.     የወረዳው ከተማ (ቂልጦ) ከአዲስ አበባ ርቀቱ 221 ኪሎ ሜትር ሲሆን 176 ኪሎ ሜትር አስፓልት እና 45 ኪሎ ሜትር ፒስታ መንገድ ነው።

 

ተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 09 27 17 59 14 /09 33 62 02 20

 

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግ በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ የፋይናንስ /ቤት

 

Save Tender