የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን የእንጦጦ ፓርክን በአገር በቀል እጽዋት መተካት ስለፈለገ በውስጡ የሚገኙ የባህር ዛፎችን በቁማቸው በመሸጥ ይፈልጋል።
የባህር ዛፍ ሽያጭ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን የእንጦጦ ፓርክን በአገር በቀል እጽዋት መተካት ስለፈለገ በውስጡ የሚገኙ የባህር ዛፎችን በቁማቸው በመሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም ባህር ዛፎቹን ቆርጦ ለመግዛት የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የቀረበውን መስፈርት ማሟላት ይጠበቅባችኋል።
1. ተጫራቾች በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
2. የባህር ዛፎቹን ለማንሳት በቂ አቅም፣ ልምድ እና የዛፍ ማስወገጃ መሳሪያ ያለው እንዲሁም ለአገር በቀል እጽዋቶች አስፈላጊውን ጥንቃቄ የሚያደርግ።
3. አሸናፊው ድርጅት ውል በገባ በአርባ አምስት ቀን ውስጥ ስራውን መጨረስ የሚችል።
4. የተቆራረጡ ቅርንጫፎች ከፓርኩ ውስጥ በራሱ ትራንስፖርትና የጉልበት ሰራተኛ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ የሚችል።
5. ዛፉ ከተቆረጠ በኋላ ድጋሚ እንዳያበቅል / እንዳያቆጠቁጥ ዲባርክ ማድረግ የሚችል።
6. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ ወይም ባንክ ጋራንቲ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
7. ዛፉ በሚወገድበት አካባቢ ሊደርስ የሚችል መሰረተ ልማት ጉዳት ማስተካከያ የሚውል የጨረታውን ከጠቅላላው መነሻ ዋጋ ሁለት በመቶ ሲፒኦ ማሰያዝ የሚችል።
8. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታው ሰነድ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ/ መገናኛ ዘፍመሽ ፊት ለፊት ታሜጋስ ህንጻ ላይ ሶስተኛ ፎቅ የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አስር ተከታታይ የስራ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ በመቅረብ መግዛት ይቻላል።
9. ተጫራቾች የጨረታው ሰነድ ፋይናንሺያል ዶክመንትና ቴክኒካል ዶክመንት ለየብቻ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሳጥኑ እስከሚታሸግበት ከ10ኛው ተከታታይ የስራ ቀናት በኋላ በአለው 11ኛው ቀን ጠዋት 4፡00 ድረስ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
10. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ በዚያው ቀን ጠዋት 4፡30 መገኛኛ ዘፍ መሽ ፊት ለፊት ባለው ታሜ ጋስ ህንጻ ላይ ሶስተኛ ፎቅ በግዢ እና ንብረት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል።
11. አሸናፊው ከተለየ በኋላ በሶስት ቀን ውስጥ ስራ መጀመር የሚችል።
12. አንድ ተጫራች ከሁለት ኮምፓርትመንት በላይ መጫረት አይችልም።
13. የጨረታ መክፈቻው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ላይ የሚውል ከሆነ በቀጣይ ሰኞ ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል።
14. ዘግይቶ የደረሰ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
15. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 09 12 47 56 09 / 09 10 85 13 75 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን
