Tender Detail

Tender Details

  • Company የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ
  • Address ሀዋሳ ከተማ ፡ ሲዳማ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 046-221-7002
  • Website
  • Deadline26 Feb 2026, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price200.00
  • opening date2026-02-26 00:00:00
  • Categories Music And Music Instrument , Electronics Materials

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የትምህርት ቢሮ ከዚህ በታች በመደበኛ በጀት በአዳራሽ ላይ የሚገጠም ድምጽ መሳሪያ ግዥ እና የኤሲ ግዥ ለማከናወን ሕጋዊ ድርጅቶችን አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ዘዴ መግዛት ይፈልጋል።


ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

ቁጥር 12/2018

 

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የትምህርት ቢሮ ከዚህ በታች በመደበኛ በጀት በአዳራሽ ላይ የሚገጠም ድምጽ መሳሪያ ግዥ እና የኤሲ ግዥ ለማከናወን ሕጋዊ ድርጅቶችን አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ ዘዴ መግዛት ይፈልጋል።

ከዚህ በላይ ለተዘረዘሩት በውድድር መስፈርት መሰረት ለመሣተፍ የሚፈልጉ

1.     በመስኩ ህጋዊ የንግድ ፈቃድና የዘመኑን ግብር የከፈሉ እንዲሁም የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው መሆን አለባቸው የተጫራቾች የአቅራቢነት ምዝገባ።

2.     ተጫራቾች ዋጋቸውን የሚገልፀውን ሰነድ በታሸገ ፖስታ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን ከቀኑ 1130 ድረስ ከግ///አስ/ ዳይሬክቶሬት ከግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 14 በአካል በመቅረብ የታደሰ ንግድ ፍቃድ በማሳየት መግዛት አለባቸው።

3.     የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን 11ኛው ቀን ከጠዋቱ 300- 600 ድረስ ብቻ ለዚህ አላማ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።

4.     ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 11ኛው ቀን 900 ሰዓት ይከፈታል። ሆኖም 11ኛው የስራ ቀን በማይሆንበት ጊዜ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ጊዜና ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።

5.     የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 90 ቀን ጸንቶ የሚቆይ ለእያንዳንዱ ሎት ለየብቻ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ/ በሲፒኦ ወይም አንኮንዲሽናል ባንክ ጋራንቲ በማቅረብ መወዳደር አለባቸው።

6.     ተጫራቾች ጨረታውን በሚወዳደሩ በፖስታ በማሽግ ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዶክመንት ለየብቻ በማድረግ ከሁለት ኮፒ ጋር ማቅረብ አለባቸው።

7.     ጨረታው 3 ወራት /90 ቀናት/ ብቻ ፀንቶ የሚቆይ ይሆናል።

8.     የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከግ///አስ/ ዳይሬክቶሬት ማግኘት ይቻላል፤ አንድ ተጫራች ከአንድ ሎት በላይ መወዳደር አይችልም።

9.     ቢሮው ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

 

ማሣሰቢያ፡- ሽያጩ ቫትን ጨምሮ ከብር 20,000.00 /ሀያ ሺህ ብር/ በላይ ሆነው ግዥ 50% ቫት ቀንስን የምናስቀር መሆኑን እንገልፃን።

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 046-221-7002/3

 

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ

Save Tender