ድርጅታችን ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በመካኒሳ የዋና መ/ቤት ህንጻ ጂ+10 እና ጂ+2 አጠቃላይ የሕንጻ ጥገና አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 005/2018 ዓ.ም
ድርጅታችን በመካኒሳ የዋና መ/ቤት ህንጻ ጂ+10 እና ጂ+2 አጠቃላይ የሕንጻ ጥገና አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም ስለሚፈልግ ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
1. የታደሰ ፍቃድና የዘመኑ ግብር ለመክፈላችሁ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
2. ቫትን አካቶ የማይመለስ ብር 500.00 /ብር አምስት መቶ/ በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነዱን መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 308 በመቅረብ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
3. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶቻችሁን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ኦርጅናል እና ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 2 በመቶ በሲፒኦ ለብቻው በኤንቨሎፕ በማሸግ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
5. ተጫራቾች የሚያቀርቧቸውን ሠነዶች እስከ የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሠዓት ድረስ መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ግዥ ቢሮ ቁጥር 503 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
6. ጨረታው በዚያው ዕለት ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
7. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
ፖ.ሣ.ቁ. 3516 ስልከ 011 369 0563 ፋክስ 011 5 513299
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
