የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የደቡብ ወሎ ዞን የኩታበር ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት በኩታበር ወረዳ 05 ቀበሌ የማህበረሰብ ደን ማለትም ባህር ዛፍና ጽድ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የደቡብ ወሎ ዞን የኩታበር ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት በኩታበር ወረዳ 05 ቀበሌ የማህበረሰብ ደን ማለትም ባህር ዛፍና ጽድ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ በዘርፉ የተሰማራ ማንኛውም ተጫራች፣
1. በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለው፡፡
2. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች በኦርጂናልና በኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
3. የሚገዛውን እቃና ዓይነት ዝርዝር መግለጫ/ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ለ15 የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ለአንድ ሎት በመክፈል ኩታበር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 6 ማግኘት ይቻላል፤
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በጥሬ ገንዘብ ወይም በሲፒ.ኦ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ከታወቀ ባንክ ኢንሹራንስ ካምፓኒ ማረጋገጫ ትእዝዝ በማቅረብ ለሚወዳደሩበት ብር .... ወይም ለሚያቀርበው ወይም በሞላው ዋጋ 10% /አስር ፐርሰንት/ የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ አለባቸው፡፡
6. ጽ/ቤቱ ጨረታውን የሚያወዳድረው በሉት ድምር ነው፣
7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ኩታበር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ንብረት አስተዳደር ቡድን በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሠዓት እስከ 16ኛው ቀን ከጧቱ 4:15 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
8. ጨረታው የሚከፈተው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ነው።
9. 16ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተገለጸው ሰዓት ጨረታው 4:30 ላይ ይከፈታል፡፡
10. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
11. ለተጨማሪ ማብራሪያ በአካል ወይም በስልክ ቁጥር 0334488001/0334480228 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የደቡብ ወሎ ዞን የኩታበር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
