ድርጅታችን የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ መካኒሳ በሚገኘው ዋና መ/ቤት የቆርኪ መክደኛ ማሽን ቤት ጣሪያ በማይካ ለማሰራት ስለሚፈልግ ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 006/2018 ዓ.ም
ድርጅታችን መካኒሳ በሚገኘው ዋና መ/ቤት የቆርኪ መክደኛ ማሽን ቤት ጣሪያ በማይካ ለማሰራት ስለሚፈልግ ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
1. የታደሰ ፍቃድና የዘመኑ ግብር ለመከፈላችሁ መረጃ ማቅረብ የምትችሉ፤
2. ቫትን አካቶ የማይመለስ ብር 500.00 /ብር አምስት መቶ/ በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነዱን መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 308 በመቅረብ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፤
3. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶቻችሁን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ኦሪጅናል እና ፎቶ ኰፒ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባችኋል፤
4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 2 በመቶ በሲፒኦ ለብቻው በኤንቨሎፕ በማሸግ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፤
5. ድርጅቱ ማሰራት የሚፈልግበትን ቦታ በአካል በመገኘት መጎብኘት እና እና ስለ ሥራው ከሚመለከተው ጋር መወያየት ይቻላል፣
6. ተጫራቾች የሚያቀርቧቸውን ሠነዶች እስከ መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሠዓት ድረስ መካኒሳ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ግዥ ቢሮ ቁጥር 503 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ጨረታው በዚያው ዕለት ከጠዋቱ 4:15 ሠዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፤
8. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ፖ.ሣ.ቁ 3516 ስልክ 011 369 0563 ፋክስ 011 5 513299
የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
