የጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ከ UNICEF በተገኘ በጀት በ2018 የተቀናጀ ትምህርት የቅድመ አንደኛ ደረጃ 1 እና 2 የመምህሩ መምሪያ ህትመት አገልግሎት ግዥ እንዲሁም የልዩ ፍላጎት ቁሳቁስ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መፈጸም ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ከ UNICEF በተገኘ በጀት በ2018 የተቀናጀ ትምህርት የቅድመ አንደኛ ደረጃ 1 እና 2 የመምህሩ መምሪያ ህትመት አገልግሎት ግዥ በግዥ በመለያ ቁጥር UNICEF/Non-con/NCB/2018/01 እንዲሁም የልዩ ፍላጎት ቁሳቁስ ግዥ በግዥ በመለያ ቁጥር UNICEF-Goods-NCB-2018-01 በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ሕጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት እንድትጫረቱ እንጋብዛለን።
1. ተጫራቾች በሚሳተፉበት የግዥ አይነት የታደሰ ንግድ ስራ ፈቃድ ንግድ ምዝገባ ወረቀት
2. ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
3. የዘመኑን ግብር ስለመክፈላቸው ከሚመለከተው የገቢ ግብር ባለስልጣን ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
4. የአቅራቢነት ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል
5. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በስራ ሰዓት ከትምህርት ቢሮ ግዥ የስራ ከፍል ቁጥር 20 በመቅረብ የማይመለስ 300.00 በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
6. ተጫራቾች የጨረታውን ዶክመንት ቴክኒካልና ፋይናንሺያል ሰነዶቻቸውን በጨረታ መመሪያው መሠረት በማያያዝ ለእያንዳንዳቸው አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ ማቅረብ አለባቸው።
7. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ የጨረታ ሰነዱን ለዚሁ በተዘገጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል። ጨረታ ሰነዱ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3:30 ተዘግቶ በ4:00 በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ ይከፈታል። ከላይ የተጠቀሱት ቀናት በዓላት ወይም ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ጨረታው የሚከፈት ይሆናል።
8. ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል መሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ አራት ኪሎ ማረሚያ ቤት ጎን
ስልክ፡- (+251) 47 551 1477
የጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ
