በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የባሕር ዳር ሪጅን የከባድ፣ መካከለኛ እና ቀላል ተሽከርካሪዎችን ለ5 ዓመት በሚቆይ ውል ተጫራቾችን አወዳድሮ የጥገና አገልግሎት ማግኘት ይፈልጋል፡፡
ለ2ኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ ኢኤአ‐ባሪ/ግብጨ/011/2018
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የባሕር ዳር ሪጅን የከባድ፣ መካከለኛ እና ቀላል ተሽከርካሪዎችን ለ5 ዓመት በሚቆይ ውል ተጫራቾችን አወዳድሮ የጥገና አገልግሎት ማግኘት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም፡-
1. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራና ብቃት ያለው ጋራዥ ጥገና ለማድረግና ለማደስ መወዳደር ይችላል፡፡
2. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራና ብቃት ያለው ድርጅት የተሟላ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመከፈል በሚከተለው አድራሻ ማግኘት ይቻላል፡፡ ባሕር ዳር ሪጅን ጽ/ቤት ቀበሌ 05 ቅ. ጊዮርጊስ ቤተ-ከርስቲያን ፊት ለፊት 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር፡ 408 ስልክ ቁጥር 058-320-69-99/6775 ባሕርዳር፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማግኘት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉ በዘርፉ ፈቃድ ያላቸው የንግድ ስራ ፈቃድ እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ማስረጃ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ አለባቸው፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ CPO፣ በባንክ ጋራንት ወይም በጥሬ ገንዘብ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ/ ማስያዝ አለባቸው፡፡
6. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ኮፒና ኦርጅናል በማለት እስከ ተጠቀሰው የጨረታው መዝጊያ ቀንና ሰዓት ድረስ በተ.ቁ 2 በተገለጸው አድራሻ ድረስ በመቅረብ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
7. ተጫራቾች ከመንገድና ትራንስፖርት ባለስልጣን የተሰጠ የስራ ብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፡፡
8. ተጫራቾች የመጫረቻ ዋጋቸውን በጨረታ ሰነዱ ላይ በተጠቀሰው መሰረት ማቅረብ አለባቸው፡፡
9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ባይገኙም በባሕርዳር ሪጅን ሰፕላይ ቼይን፣ ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ቁጥር 408 መጋቢት 07 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ይከፈታል።
10. ሪጅኑ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የባሕር ዳር ሪጅን
