የደባርቅ ከተማና አስተዳደር ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በ 2018 በጀት ዓመት ለጽ/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ በሎት አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የደባርቅ ከተማና አስተዳደር ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በ 2018 በጀት ዓመት ለጽ/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ በሎት አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
ስለዚህ፡-
- ሎት 1- የመኪናና የማሽነሪ መለዋወጫ (ስፔርፓርት) እቃዎች፣
- ሎት 2 - የማሽነሪ እና የመኪናዎች ጎማና ባትሪ
ስለዚህ ተጫራቾች ሊያሟሉት የሚገባቸው፡-
1. ህጋዊ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው፣
2. ቲን ነበር ያላቸው፣
3. የግዥ መጠን ብር 200.000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናቶች በመንግስት የስራ ሰዓት የጨረታ ሰነዱን በብር 100 /አንድ መቶ ብር/ መግዛት ይቻላል፡፡
5. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ለሚጫረቱበት ጨረታ በየሎቱ በእያንዳንዱ ማለትም ለሎት 1- የማሸነሪና መኪና መለዋወጫዎች ስፔርፖርት ግዥ 30,000 ብር፣ ለሎት 2 ጎማና ባትሪ ግዥ 20,000 ብር ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ በጥሬ ገንዘብ በመ/ቤቱ በመሂ 1 የተቆረጠ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሌተርኦፍ ክሬዲት ሆኖ መረጃውን ፖስታው ውስጥ አስገብተው የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው፡፡
6. የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 13 በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታተመ ጊዜ ጀምሮ በ16ኛ ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ድረስ ወይም ከዚያ በፊት አንድ ኦርጅናልና አንድ ፎቶ ኮፒ በታሸገ ፖስታ ከጨረታ ሳጥኑ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
7. የመጫረቻ ሰነዱ ዋጋ ፀንቶ የሚቆየው ጊዜ 40 የስራ ቀናቶች ይሆናሉ፡፡
8. ጨረታው ቢሮ ቁጥር 13 በተገለጸው ቦታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታተመ ጊዜ ጀምሮ በ16ኛ ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም ባይገኙ ከቀኑ በ4፡30 ሰዓት ጨረታው ይከፈታል በ16ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
9. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የዕቃ ዓይነት ዝርዝር ከሚገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዕቃ ዝርዝር መረዳት ይችላሉ።
10. አሸናፊው ድርጅት ንብረቱን ደባርቅ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ፅ/ቤት ቢሮ ቁጥር 13 ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይኖርባቸዋል፡፡
11. ተጫራቾች ሰነዱን በሚሞሉበት ሰዓት ስርዝ ድልዝ መኖር የሌለበት ሲሆን የእቃው ናሙና ቢሮ ቁጥር 13 በግንባር በመቅረብ ማየት ይኖርባቸዋል፡፡
12. ተጫራቾች የሚያቀርቡ የመወዳደሪያ ሀሳብ ላይ ሙሉ ስማቸውን ፊርማቸውን በሙሉ አድራሻቸውን ማስፈርና የድርጅቱን ማህተም ማድረግ አለባቸው።
13. ጨረታው በሎት ጠቅላላ ድምር ዝቅተኛ ዋጋ ሙሉ በሙሉ በሞላ ስለሆነ ከመጫረቻ የዋጋ መሙያ ሰነዱ ላይ ከፍት ማድረግ የለባችሁም በተጨማሪም የዕቃዎች ብዛት ከበጀት አንፃርሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
14. መ/ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
15. በጨረታውን ለመሳተፍ የሚፈልጉ አቅራቢዎች ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልጋቸው በስልክ ቁጥራችን 058 117 0033 ወይም 0581174208 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ፡- ሁሉም ዕቃዎች ጥራቱን የጠበቀና በተጠየቀው ሞዴል መሰረት ኦርጅናል መሆን አለባቸው።
ተጨማሪ ማብራሪያዎች መረጃዎች ካሉ በቢሮአችን በውስጥ - ሰሌዳ ማስታወቂያ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የደባርቅ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት
