በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ሐርረጌ ቅ/ጽ/ቤት በዲንዲን ዲስትሪክት የሚገኙትን ያገለገሉ የተለያዩ ብረታ ብረቶችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሚወገዱ አሮጊ ብረታ ብረት ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር OFWEHB/MM-01/2018
በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ሐርረጌ ቅ/ጽ/ቤት በዲንዲን ዲስትሪክት የሚገኙትን ያገለገሉ የተለያዩ ብረታ ብረቶችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም
1. የብረታ ብረት እና ተዛማች ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የቫት ("VAT”) ተመዝጋቢና "TIN number" ያላቸው ድርጅቶች እና ግለሰቦች እንዲሁም ስለ ጨረታው ዝርዝር ሁኔታ የሚገልፅ የጨረታ ሰነድ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ጭሮ ከተማ ም/ሐርረጌ ዞን ውሃ እና ኢነርጂ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ከሐርረጌ ቅ/ጽ/ቤት በመግዛት በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ ።
2. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል።
3. ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ትክክለኛው ቀንና ሰአት በጨረታው ሰነድ ውስጥ ይገለጻል።
4. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid bond) የሚሆን ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 5% በማስላት ጭሮ ከተማ ውስጥ በሚገኙት ባንኮች በባንክ በተረጋገጠ ደረሰኝ (cpo) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
5. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-0255512767/0255512239 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት የሐረርጌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
