የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃ እና አገልግሎቶች በግልጽ ጨረታ የግዥ ዘዴ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 012/2018
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃ እና አገልግሎቶች በግልጽ ጨረታ የግዥ ዘዴ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም:- ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
· በዘርፉ ለዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለው
· የንግድ ምዝገባ
· የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት
· የቫት ሰርተፍኬት
· በመንግስት ግዥ በአቅራቢነት የተመዘገበ
ሎት 1. wifi access point (router) የጨረታ ማስከበሪያ መጠን 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር)፣ ሎት 2. የመኪና ኪራይ አገልግሎት (ለመካከለኛ አመራሮች) ለስድስት ወራት በውል የሚፈጸም የጨረታ ማስከበሪያ መጠን 100.000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር)፣ ሎት 3 የመኪና ኪራይ አገልግሎት (ለገበያ እና ለተሰብሳቢ ሂሳብ ሰራተኞች አገልግሎት) ለስድስት ወራት በውል የሚፈጸም የጨረታ ማስከበሪያ መጠን 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር)
· በሲ.ፒ.ኦ፣ ቢድ ቦንድ ወይም ለጥቃቅንና አነስተኛ ከአደራጃቸው አካል የሚሰጥ የዋስትና ደብዳቤ በማያያዝ ይህ ጨረታ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 15 ተከታታይ ቀናት አንደኛ ፎቅ በሚገኘው አቅርቦት መምሪያ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ቴክኒካል ዶክመንት ዋና እና ቅጂ እንዲሁም የሚወዳደሩበትን ዋጋ ዋና እና ቅጂ በሚል በጉልህ በሚታይ መልኩ በመጻፍና የሚወዳደሩበትን ሎት በፖስታዎቹ ላይ በመግለጽ በአራት የተለያየ ፖስታ በማሸግ በእንድ ኤንቨሎፕ በማድረግ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
· በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ 100 ብር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
· ስርዝ ድልዝ ያለውና ያልተፈረመ እንዲሁም በጉልህ የማይታይ አጠራጣሪ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
· ጨረታው በ16ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አቅርቦት መምሪያ 1ኛ ፎቅ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን የተጫራቹ አለመገኘት ጨረታውን ከመከፈት ኢያስተጓጉለውም፡፡ የጨረታ መክፈቻው ቀን እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ ባለው የሥራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፡፡
· ድርጅታችን አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አራት ኪሎ ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ፊት ለፊት
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
