የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ግብርና ቢሮ የማር እና የእንሰት ማቀነባባሪያ ማሽኖች ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የማር እና የእንሰት ማቀነባባሪያ ማሽኖች ግዥ
ጨረታ ቁጥር 124/18
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ግብርና ቢሮ የማር እና የእንስሳት ማቀነባባሪያ ማሽኖች ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
መለኪያ |
ሎት |
ብዛት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
የሚታሸግበት ሰዓት |
የሚከፈትበት ሰዓት |
|
1. |
የማር ማቀነባበሪያ ማሽን ግዥ (አቅርቦት፤ ተከለ፤ ኮሚሽን፤ ስልጠናን) አካትቶ |
በሴት |
ሎት 1 |
3 |
105,000 |
9:00 |
9:05 |
|
2. |
የእንስሳት ማቀነባበሪያ ማሽን ግዥ (አቅርቦት፤ ተከላ፤ ኮሚሽን፤ ስልጠናን) አካትቶ |
በሴት |
ሎት 2 |
1 |
120,000 |
10:00 |
10:05 |
መሟላት ያለባቸው ግዴታዎች
· በስራ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት ሰነዶችን ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች በጨረታዉ መሳተፍ ይችላሉ።
· ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ለ45 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል።
· በተጫራቾች የሚያቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ ፤ በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና፤ በካሽ ያስያዙበት ማቅረብ አለባቸው።
· ተጫራቾች በቢሮው የተዘጋጀውን መደበኛ የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን 19/07/2018 ዓ.ም 9፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 200 ለሰነድ በመክፈል ዱራሜ ከተማ በሚገኛው የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 003 መዉሰድ ይችላሉ።
· ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ (ፕሮፎርማ) በመሙላት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 28/7/2018 ዓ.ም ሎት 01 ከቀኑ 9፡00 ሰዓት እንዲሁም ሎት 02 ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ የቴክኒካልና ፋይናንሻል የመጫረቻ ሠነዶችን በአንድ ፖስታ በማዘገጃት በቢሮው የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 003 ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
· የጨረታው ሳጥን በቀን 28/7/2018 ዓ.ም ሎት 1 ከቀኑ 9፡00 ታሽጎ 9፡05 ሰዓት እንዲሁም ሎት 02 ከቀኑ 10፡00 ታሽጎ 10፡05 ሰዓት /ተወካዮቻቸው በተገኙበት በቢሮው የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 003 ይከፈታል፡፡
· ቢሮው ለዚህ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ
