በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ስር የሚገኘው የነጌሌ ቦረና መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጽ/ቤት 45 /አርባ አምስት/ እና ከዚያ በላይ ሰው መያዝ የሚችል አንድ (1) ለሠራተኞች ሰርቪስ አገልግሎት የሚሆን የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፡፡
የሠራተኞች ሰርቪስ መኪና ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ስር የሚገኘው የነጌሌ ቦረና መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጽ/ቤት 45 /አርባ አምስት/ እና ከዚያ በላይ ሰው መያዝ የሚችል አንድ (1) ለሠራተኞች ሰርቪስ አገልግሎት የሚሆን የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፡፡
ከላይ በተገለፀው መሠረት ጨረታውን መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
1. የ2018 ዓ.ም የታደለ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያለው ያላት።
2. የዘመኑን የስራ ግብር የከፈለ የከፈለች።
3. የVAT 15% ወይም TOT 3% ተመዝጋቢ የሆነ/የሆነች እና የግብር መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት ያለው/ያላት።
4. ኦርጅናል ሊብሬ ከእነ ኮፒው ማቅረብ የሚችል የምትችል።
5. የዓመቱን ቦሎ፤ 3ኛ ወገን ኢንሹራንስ የለጠፈ ያለው ያላት።
6. የድርጅቱን ሠራተኞች ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ባሉት የስራ ቀናት ውስጥ በመንግስት የስራ ሠዓት መግቢያ እና መውጫ ሰርቪስ ለመስጠት የሚፈልግ፡፡ በቀን 4 ምልልስ ይሆናል።
7. የመኪናው ወንበሮች ምቹ የሆኑ፤ ወለሉ እና ጣሪያው ዝናብ እና አቧራ የማያስገባ፤
8. መስታዎቶቹ ያልተሰበሩ፤ መስኮቶቹ በደንብ የሚከፈት የሚዘጋ እና በሚገባ አየር የሚያስገባ።
9. የኪራይ ሁኔታ ለ1 (አንድ) ዓመት ሆኖ እየታየ የሚታደስ ይሆናል።
10. የነዳጅ፣ የሹፌር እና የጥገና ወጪ በባለንብረቱ የሚሸፈን ይሆናል።
11. አሸናፊው ድርጅት ውል ገብቶ ስራ ከጀመረበት ወር ጀምሮ በመንግስት የሚጨመር የነዳጅ ጭማሪ የታሪፍ ልዩነቱን መ/ቤቱ በኪሜትር አስልቶ የሚከፍል ይሆናል፡፡ ከላይ የተጠቀሱትን ህጋዊ ማስረጃዎች ማቅረብ የሚችል /የምትችል/ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ አስራ አምስት (15) ቀናት ጨረታው አየር ላይ የሚውል ስለሆነ መሳተፍ ይቻላል።
12. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በራሳችሁ ህጋዊ የዋጋ ማቅረቢያ (ፕሪፎርማ) በመሙላት በታሸገ ፖስታ (ኤንቨሎፕ) ታሽጎ ይህ ጨረታ አየር ላይ ከዋለበት ቀን አንስቶ የሚቆጠር እስከ 15 ተኛው ቀን 11፡30 ሰዓት ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት ዶሎ በር ኬላ አጠገብ በሚገኘው መ/ቤታችን ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት አስተዳደር ክፍል ማቅረብ የምትችሉ ሲሆን 15 ተኛው ቀን ልክ 11፡30 ሰዓት ጨረታው ዝግ ተደርጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማግስቱ ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል።
13. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ
· ከላይ የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ማቅረብ የማይችሉ ተጫራቾች ዝቅተኛ የመጫረቻ ዋጋ ቢያቀርቡም በጨረታው መመሪያ መሠረት አሸናፊ መሆን የማይችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
· የጨረታው መክፈቻ እና መዝጊያ ቀን የበዓል እና የእረፍት ቀናት ከሆነ በቀጣይ በሚኖረው የስራ ቀናት የሚከፈት መሆኑን እናሳውቃለን።
ለበለጠ መረጃ
ስልክ ቁጥር 0464451707/0988080497 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
አድራሻ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ነጌሌ ቦረና ቅርንጫፍ 03 ቀበሌ
ዶሎበር ኬላ መውጫ
የኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት
