በመንግሥት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የምዕራብ ሪጅን ጽ/ቤትና በሥሩ ያሉ ቅ/ጽ/ቤቶችና መስክ ጽ/ቤቶች 1. የጽሕፈት መሣሪያዎች 2. የቢሮ ማሽነሪ ጥገና 3. የጽዳት ዕቃዎች እና 4. የህትመት ሥራዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ለ 2ኛ ዙር የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በመንግሥት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የምዕራብ ሪጅን ጽ/ቤትና በሥሩ ያሉ ቅ/ጽ/ቤቶችና መስክ ጽ/ቤቶች 1. የጽሕፈት መሣሪያዎች 2. የቢሮ ማሽነሪ ጥገና 3. የጽዳት ዕቃዎች እና 4. የህትመት ሥራዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ ተወዳዳሪዎች፡-
1. በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣በአገር ዉስጥ ገቢ የድጋፍ ደብዳቤ፣ የአቅራቢዎች የምዝገባ የምስክር ወረቀት፤Tin No. ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የቫት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ እንዲሁም ለጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ ብር 3,000.00 (ሶስት ሺህ) በሰርቲፋይድ ቼክ(CPO) ለማስያዝ የሚችሉ ተጫራቾች የተዘጋጀዉን የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ) በመክፈል ከቢሮ ቁጥር 7 (ሰባት) በመውሰድ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እስከ 11፡00 ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት የምትችሉና የጨረታ ሰነዱን ወይም ዋጋቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ በሁለት ኮፒ በማሸግ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
2. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ11ኛው ቀን ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በ8፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ 11ኛው ቀን ቅዳሜ /እሁድ ወይም በዓል ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል፡፡
3. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት በጽሕፈት መሳሪያዎች በጽዳት ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ አለባቸው፡፡
4. ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ ያለመገኘት የጨረታዉን ሂደት አያስተጓጉልም፡፡
5. ተጫራቾች ባሸነፉት የዕቃዎች ዋጋ ለውል ማስከበሪያ 10% ማስያዝ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
6. መ/ቤቱ የተሻለ የአሰራር ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድረሻ፡- ምስራቅ ወለጋ ዞን ፖሊስ መመሪያ ፊት ለፌት ዉጋገን አጠገብ ነው፡፡ ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 057 661 2054/057 661 5178
የመንግሥት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ምዕራብ ሪጅን ጽ/ቤት
