በኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወሰነ አሰላ ብቅል ፋብሪካ በጎተራ ተከማችቶ የሚገኘውን 5,000 /አምስት ሺህ/ ኩንታል 3ኛ ደረጃ ብጣሪ ገብስ /ተረፈ ምርት/ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የ3ኛ ደረጃ ብጣሪ ገብስ የሽያጭ ጨረታ
የጨረታ ቁጥር OACF-AMF/MBSMD/03/2018
በኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወሰነ አሰላ ብቅል ፋብሪካ በጎተራ ተከማችቶ የሚገኘውን 5,000 /አምስት ሺህ/ ኩንታል 3ኛ ደረጃ ብጣሪ ገብስ /ተረፈ ምርት/ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎትና አቅም ያላቸው ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው፡፡
1. ተጫራቾች የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN No./ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
2. በእህል ንግድ ወይንም የከብቶች መኖ በማዘጋጀት ወይም ተመሳሳይ ሥራ ሕጋዊ የሆነ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፡፡
3. የጨረታ ሠነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር ብቻ) በፋብሪካችን አካውንት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000257808697 ወይም በኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ 1000043405229 በመክፈል/ገቢ በማድረግ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ጠዋት 2፡00-6፡00 ከሰዓት በኋላ ከ7፡00-10፡00 ሰዓት ቅዳሜ ጠዋት 2፡00- 6:00 ሰዓት ድረስ አሰላ /ቁሉምሳ/ በሚገኘው ፋብሪካችን ቢሮ ቁጥር 051 ወይንም አዲስ አበባ በሚገኘው ዋና መ/ቤት ከጀርመን አደባባይ ወደ ሚካኤል አደባባይ በሚወሰደው መንገድ ላይ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ህንፃ ስድስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 ሠነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 400,000.00 (አራት መቶ ሺህ) በባንክ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.ኦ /C.P.O/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
5. ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በአየር ላይ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡
6. ተጫራቾች በኢንቨሎፕ የታሸገ የጨረታ ሠነዳቸውን በአሰላ ብቅል ፋብሪካ ቢሮ ቁጥር 051 በተቀመጠው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
7. ጨረታው በዕለቱ ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ በ8፡10 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አሰላ /ቁሉምሳ/ በሚገኘው የፋብሪካችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
8. የጨረታ ሳጥኑ ከታሸገ በኋላ ጨረታ ሠነዳቸውን የሚያቀርቡ ተጫራቾች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
9. ፋብሪካው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ፣
ስልክ ቁጥር፡- 0965650461 ወይም 022 331 81 97 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተ. አሰላ ብቅል ፋብሪካ
